Get Mystery Box with random crypto!

ከአንጋፋ መምህራን የደረጃ እድገት ጋር በተያያዘ ያቀረበዉ ጥያቄ እስካሁን ምላሽ አለማግኘቱን የአዲ | AHADU RADIO FM 94.3

ከአንጋፋ መምህራን የደረጃ እድገት ጋር በተያያዘ ያቀረበዉ ጥያቄ እስካሁን ምላሽ አለማግኘቱን የአዲስ አበባ መምህራን ማህበር ገለፀ፡፡
ማህበሩ ከዚህ ቀደም በሰጠዉ መግለጫ የአንጋፋ መምህራን የደረጃ እድገትን በተመለከተ በተደጋጋሚ ጊዜ ለሚመለከተዉ አካል ጥያቄዎችን ቢያቀርብም ምላሽ ባለማግኘቱ እስከ ጠቅላይ ሚንስትር ፅህፈት ቤት ድረስ ጥያቄ ለማቅረብ መዘጋጀቱን መግለፁ ይታወሳል፡፡ በአሁኑ ወቅትም ጉዳዩን ለኢትዮጵያ መምህራን ማህበር መተላለፉ እና እንደ ከዚህ በፊቱ ምላሹ የሚዘገይ ከሆነ ወደ በላይ አካል የመምህራኑን ጥያቄ ማቅረባቸው እንደማይቀር የተናገሩት የአዲስ አበባ መምህራን ማህበር ፕሬዝደንት አቶ ድንቃለም ቶሎሳ ናቸዉ፡፡
ፕሬዝደንቱ አክለዉም ለሀገር ባለዉለታ የሆኑ አንጋፋ መምህራን ምንም አይንት የደመወዝ እና የደረጃ እድገት ሳይሰጣቸዉ ጡረታ ለመዉጣት እየተገደዱ ሲሆን ይህ ደግሞ ዉለታቸዉን ማቅለል በመሆኑ ጥያቄዉ በአፋጣኝ ምላሽ ሊሰጠዉ ይገባል ሲሉም ጠይቀዋል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24