Get Mystery Box with random crypto!

በሱዳን የሁለቱ ተዋጊ ሀይሎች ዳግም የተኩስ አቁም ድርድር ማቀዳቸው ተሰምቷል፡፡ የአል አረቢያ ቴሌ | AHADU RADIO FM 94.3

በሱዳን የሁለቱ ተዋጊ ሀይሎች ዳግም የተኩስ አቁም ድርድር ማቀዳቸው ተሰምቷል፡፡
የአል አረቢያ ቴሌቪዢን ቻናል ባሰራጨው የትናንት ቀትር መረጃው ሁለቱ የሱዳን ተዋጊ አንጃዎች በሳዑዲ አረቢያና በአሜሪካ አደራዳሪነት ለዳግም የተኩስ አቁም ድርድር መጋበዛቸው ታውቋል፡፡
ሁለቱ ወገኖች ቀድሞ ለአንድ ሳምንት ከዘለቀው የተኩስ አቁም ስምምነት በኃላ ለተጨማሪ አምስት ቀናት የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ መድረሳቸው ቢነገርም በመሃል ግን በአየርና በምድር ወደ ቀደመው ከባድ ጦርነት መመለሳቸው ይታወቃል፡፡
አሁንም ሁለቱ ተዋጊ ሀይሎች ከካርቱምና ከሌሎቹም ከተሞች ጦርነት እጃቸውን ሰብሰበው ይቀመጡ ዘንድ ከአሜሪካና ከሳዑዲ አረቢያ መንግስታት ጥሪ ቀርቦላቸዋል፡፡
የሱዳን ጦር ሀይልና የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ሀይሎች ቀጥተኛ ባልሆነ መንገድ እንዲወያዩ ግብዣ ቀርቦላቸዋል ቢባልም ከሁለቱም ወገኖች የተሰጠ አስተያየት የለም ሲል የአሜሪካ ድምጽ ዘግቧል፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24