Get Mystery Box with random crypto!

በመቀሌ ኢንደስተሪ ፓርክ ዉስጥ ተሰማርተዉ የነበሩ የዉጭ ባለሃብቶችን ዳግም ወደ ስራ እንዲገቡ ለማ | AHADU RADIO FM 94.3

በመቀሌ ኢንደስተሪ ፓርክ ዉስጥ ተሰማርተዉ የነበሩ የዉጭ ባለሃብቶችን ዳግም ወደ ስራ እንዲገቡ ለማደረግ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑ ተገለፀ፡፡
በሰሜኑ ክፍል በነበረዉ ጦርነት ምክንያት ችግር ዉስጥ የነበረዉ የመቀሌ ኢንደስተሪ ፓርክን አሁን ላይ ወደ ስራ ለማስገባት የተለያዩ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን ከነዚህም ዉስጥ በጦርነቱ ምክንያት ወደ ሀገራቸዉ የገቡ የዉጭ ባለሀብቶችን ወደ ክልሉ ተመልሰዉ ዳግም ስራ እንዲጀምሩ እና በተለያዩ ዘርፎች ኢንቨስት እንዲያደርጉ ለማድረግ ስራዎች እየተሰሩ መሆኑ ነዉ የተገለፀዉ፡፡
ከቀዳሚ ስራዎች መካከልም የባለሀብቶቹን የንብረት ጉዳት መጠን እና የደረሰዉን ዉድመት ማጥናት አንዱ ሲሆን በዚህም በተገኘ ዉጤት ፓርኩ ምንም አይነት ጉዳት እንዳልደረሰበት እና የተጎዳ ንብረትም አለመኖሩን ወደ ስፍራዉ የተላከ ልኡ ክቡድን ማረጋገጡን የገለጹት በኢንደስተሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬ የኮርፖሬሽኑ ፅህፈት ቤት ሃላፉ አቶ ፍፁም ከተማ ናቸዉ፡፡
ይህንን ዉጤት በመከተልም ባለሃበቶች እንዲመለሱ የሚያደርጉ ዉይይቶች ሲደረጉ መቆየታቸዉንና በዚህም ተመልሰዉ ወደ ስራ ለመግባት ፍላጎት ያሳዩ የዉጭ ባለሀብቶች መኖራቸዉን አቶ ፍጹም አስታዉቀዋል፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24