Get Mystery Box with random crypto!

የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ሀይሎች በካርቱም የሚገኘውን ሙዚየም መቆጣጠራቸው ተገልጿል፡፡ የሙዚየሙ ምክትል | AHADU RADIO FM 94.3

የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ሀይሎች በካርቱም የሚገኘውን ሙዚየም መቆጣጠራቸው ተገልጿል፡፡
የሙዚየሙ ምክትል ዳይሬክተር በሰጡት ማብራሪያ የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ሀይሎች በካርቱም የሚገኘውን እና ትልቁን ሙዚየም መቆጣጠራቸውን አስታውቀው በውስጡ የሚገኙትን ቅርሶች ይጠብቁና ይንከባከቡ ዘንድ አግባብተዋቸዋል ነው የተባለው፡፡
ከባለፈው ሚያዝያ አጋማሽ ጀምሮ ከሀገሪቱ ጦር ሀይል አባላት ጋር ሲዋጉ የነበሩት የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ሀይሎች ሙዚየሙን የተቆጣጠሩት ባሳለፍነው አርብ መሆኑም ነው የተሰማው፡፡
የፈጥኖ ደራሽ ሀይሎቹ ሙዚየሙን ከተቆጣጠሩ በኋላ በለቀቁት የምስል መረጃ በሙዚየሙ ላይ አንዳች ጉዳት እንዳልደረሰና ሙዚየሙን ለመጎብኘት የሚፈልጉ ካሉም በሰላም መጥተው መጎብኘት እንደሚችሉ ገልጸዋል፡፡
በሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ሀይሎች እጅ የገባው ሙዚየም የጥንታዊ የሰው ቅሪተ አካል ጨምሮ በርካታ ቅርሶችን የያዘ እንደሆነ የዘገበው አልአረብያ ነው፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24