Get Mystery Box with random crypto!

የግብጽ ድምበር ጠባቂዎች በእስራኤል ጦር ሀይል ላይ ጥቃት መሰንዘራቸው ተነግሯል፡፡ የግብጽ ድምበር | AHADU RADIO FM 94.3

የግብጽ ድምበር ጠባቂዎች በእስራኤል ጦር ሀይል ላይ ጥቃት መሰንዘራቸው ተነግሯል፡፡
የግብጽ ድምበር ጠባቂ ፖሊሶች ተኩስ ከፍተው ሶስት የእስራኤል ወታደሮች መግደላቸው ሲገለጽ በሁለቱም ሀገራት ከፍተኛ ባለስልጣናት ዘንድ ድንጋጤን ፈጥሯል ነው የተባለው፡፡
የግብጽ ድምበር ጠባቂ ፖሊሶች ተኩሱን የከፈቱት በእስራኤል ምድር መሆኑን እና ምክንያቱ እንዳልታወቀ ተዘግቧል፡፡
የእስራኤል ጦር ሀይል ባወጣው መግለጫ የሁለቱ ሀገራት መንግስታት ምክንያቱን ለማዎቅ በጋራ ምርመመራ መጀመራቸውን አስታውቋል፡፡
ግብጽ በመካከለኛው ምስራቅ ቀጠና በእስራኤል እና በኢራን በሚደገፉት ታጣቂ ሀይሎች መካከል ሰላምና ጸጥታ ይሰፍን ዘንድ በዲፕሎማሲው ረገድ ጥረት የምታደርግ ሀገር መሆኗ ይታወቃል፡፡ ከእስራኤል ጋር የሰላም ስምምነት በመፈራረም ረገድም የመጀመሪያዋ የአረብ ሀገር ናት፡፡
ባሳለፍነው ቅዳሜ የግብጽ የድምበር ጠባቂ ፖሊሶች የፈጸሙት ጥቃት ምናልባትም ለሁለቱ ሀገራት ግንኙነት ዳግም መሻከር ምክንያት እንዳይሆን የሚል ስጋት መኖሩን የዘገበው ዲፌንስ ኦፍ ዴሞክራሲስ ነው፡፡
አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ፌስቡክ: https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24