Get Mystery Box with random crypto!

የቻይና ከፍተኛ ልዑክ ዩክሬንና ሩሲያን ሊጎበኝ ነው ተባለ፡፡ ልዑኩ ለዩክሬን ቀውስ መፍትሄ ለማበ | AHADU RADIO FM 94.3

የቻይና ከፍተኛ ልዑክ ዩክሬንና ሩሲያን ሊጎበኝ ነው ተባለ፡፡

ልዑኩ ለዩክሬን ቀውስ መፍትሄ ለማበጀት ሰላማዊ ተልዕኮ ይዘው ወደ ዩክሬን፣ ሩሲያ እና ሌሎች የአውሮፓ ሀገራት ጉዞ ያደርጋሉ ነው የተባለው፡፡
በሩሲያ የቀድሞ የቻይና አምባሳደር የነበሩት ሊ ሁይ ጦርነቱ ከተጀመረ በኋላ የክሬንን የሚጎበኙ የመጀመሪያው ከፍተኛ የመንግስት ተወካይ ናቸው ተብሏል፡፡
ልዑኩ ዩክሬንን ዛሬና ነገ ይጎበኛሉ ሲል የዩክሬን መንግስት ባለስልጣን ለሮይተርስ ተናግሯል ነው የተባለው፡፡
ጉብኝቱ ባሳለፍነው ሚያዝያ የቻይናው ፕሬዝዳንት ከዩክሬኑ አቻቸው ጋር የስልክ ንግግር ማድረጋቸውን ተከትሎ እንደሆነ ተነገሯል፡፡

የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት የስልክ ውይይቱን ረጅምና ትርጉም ያለው ውይይት አንደነበር በትዊተር ገጻቸው ገለጸውታል ተብሏል፡፡ ቻይና ካሳለፍነው ወርሃ የካቲት ጀምሮ ለዩክሬን ቀውስ ፖለቲካዊ መፍትሄ ይሆናል ያለችውን ባለ አስራ ሁለት ነጥብ የመፍትሄ ሀሳብ አቅርባለች ሲል ሮይተርስ ዘግቧል፡፡

አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት በ7545 አጭር የፅሁፍ መልክት ይላኩ
ድህረ ገጽ፡- https://ahaduradio.com/
ዩትዩብ፦ http://shorturl.at/cknFP
ፌስቡክ:https://www.facebook.com/ahaduradio
ትዊተር፦https://twitter.com/ahadu_radio?lang=en
አሐዱ ራድዮ 94.3 እና ቴሌቪዥን #አሐዱ_24