2022-03-26 14:08:45
ኢትዮጵያ እና ጅቡቲ አዳዲስ የአትክልትና ፍራፍሬ ምርቶችን ለጂቡቲ ገበያ ለማቅረብ ተስማሙ
የመጀመሪያው የኢትዮ-ጅቡቲ የአትክልትና ፍራፍሬ ፎረም በአዲስ አበባ ተካሂዷል።
የኢትዮጵያ ፍራፍሬና አትክልት ላኪዎች ከ20 በላይ ጥራት ያላቸውን ምርቶች ለጅቡቲ ገበያ ለማቅረብ ተስማምተዋል።
በኢትዮጵያ ሆርቲካልቸር አምራች ላኪዎች ማኅበር የተዘጋጀው የቢዝነስ ለቢዝነስ ውይይት ክፍተቶችን ለመገምገም እና ወደ ጅቡቲ የሚላኩ የአትክልትና ፍራፍሬ ምርቶችን ለማሻሻል ጠቃሚ መድረክ ሆኖ አገልግሏል።
በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኢምባሲ አቶ ቢንያም ኤፍሬም፣ ከጅቡቲ ንግድ ምክር ቤት አቶ ሲያድ አሊ ሀሰን እና አቶ ቴዎድሮስ ዘውዲ የአትክልትና ፍራፍሬ አምራች ላኪዎች ማህበር ወደ ጅቡቲ የሚላከውን ምርት ለማሳደግ የሚያስችሉ አሰራሮችን ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
በተለይ አሁን ባለው የአለም የምግብ ቀውስ ወቅት የክልላዊ ንግድን ማጠናከር እንደሚያስፈልግ ተገልጿል።
የጅቡቲ የልዑካን ቡድን በመጪዎቹ በቅርቡ በቢሾፍቱ እና በቆቃ እርሻዎችን ጉብኝት እንደሚያደርግ ይጠበቃል።
@Addis_Tv
2.4K views11:08