Get Mystery Box with random crypto!

አዲስ ቲቪ Adiss Tv AMN

የቴሌግራም ቻናል አርማ addis_tv — አዲስ ቲቪ Adiss Tv AMN
የቴሌግራም ቻናል አርማ addis_tv — አዲስ ቲቪ Adiss Tv AMN
የሰርጥ አድራሻ: @addis_tv
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 8.17K

Ratings & Reviews

4.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-11-15 23:00:48 የስም ዝርዝሮቹ ብዛት ስላላቸው
በቀላል መንገድ ሚፈልጉትን ስም
ለማግኝት search የሚለውን
በመጫን ሚፈልጉትን ስም ያስገቡ::
2.4K views20:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-01 17:06:02
500 ሜትሪክ ቶን አስቸኳይ የሰብዓዊ ድጋፍ ትግራይ ክልል ደረሰ

500 ሜትሪክ ቶን አስቸኳይ የምግብ ድጋፍ በዛሬው እለት ትግራይ ክልል መድረሱን የአለም ምግብ ድርጅት ገለጸ።

ወደ ክልሉ በየብስ የሚደረገው የሰብአዊ ድጋፍ እንቅስቀሴ መጀመሩን ተከትሎ ሰፊ ስትራቴጂካዊ ውጤት እያስገኘ መሆኑን ድርጅቱ አስታውቋል።

በዛሬው እለትም 500 ሜትሪክ ቶን አስቸኳይ የምግብ ድጋፍ በድርጅቱና
አጋር አካላትአማካኝነት ወደ ክልሉ መድረሱን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

መንግስት በትግራይ ክልል ያለው የሰብአዊ ድጋፍ በተጠናከረ ሁኔታ እንዲቀጥል የግጭት ማቆም ውሳኔ ማድረጉና በየብስ የሚደረገው ድጋፍም እንዲቀጥል መወሰኑ ይታወቃል።

@Addis_Tv
8.8K views14:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-31 16:40:37
በአፋር ክልል በአብኣላ በኩል እርዳታ ወደ ትግራይ ክልል መጓጓዝ ጀመረ

በዓለም ምግብ ድርጅት አማካይነት 21 ከባድ የጭነት መኪናዎች የእርዳታ እህል በመጫን በአፋር ክልል በአብኣላ በኩል የሰብዓዊ እርዳታ በየብስ ትራንስፖርት ወደ ትግራይ ክልል ማጓጓዝ መጀመሩን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ።

የኢትዮጵያ መንግስት በትግራይ ክልል ውስጥ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ያሉ ዜጎችን ህይወት ለመታደግ ሁሉንም አማራጮች በመጠቀም የሰብዓዊ እርዳታን ለማቅረብ እንቅስቃሴ መጀመሩ የሚታወስ ነው፡፡

ውሳኔው ከተወሰነበት ቀን ጀምሮ የመድኃኒት፣ የህክምና መሳሪያዎች፣ ገንዘብና አልሚ ምግቦችን ረጂ ድርጅቶች በቻሉት መጠን በአየር ትራንስፖርት በየዕለቱ ማጓጓዝ መጀመራቸውን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት በላከው መግለጫ አመላክቷል፡፡

በዛሬው ዕለትም በዓለም ምግብ ድርጅት አማካይነት 21 ከባድ የጭነት መኪናዎች የእርዳታ እህል በመጫን በአፋር ክልል በአብኣላ በኩል የሰብዓዊ እርዳታ በየብስ ትራንስፖርት ወደ ትግራይ ክልል ማጓጓዝ መጀመራቸውን ነው ያስታወቀው፡፡

የኢትዮጵያ መንግስት የሰብዓዊ እርዳታ ለሚያስፈልጋቸው ዜጎች የሰብዓዊ ድጋፍ አቅርቦቱን በተሟላ ሁኔታ ለማስኬድ ከተባበሪና ባለድርሻ አካላት ጋር ለመስራት ዛሬም ቁርጠኛ መሆኑንም አጽንኦት ሰጥቷል፡፡

@Addis_Tv
7.0K views13:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-31 16:38:43 ከነገ ጀምሮ ለነባር እና ለአዳዲስ የሃይማኖት ቴሌቪዥን አመልካቾች ፈቃድ መስጠት ሊጀመር ነው

ከመጋቢት 23 2014 ዓ.ም ጀምሮ ለነባር እና ለአዳዲስ የሃይማኖት ቴሌቪዥን አመልካቾች ፈቃድ መስጠት እንደሚጀምር የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ገለጸ።

ባለስልጣኑ በሃይማኖት ብሮድካስት ረቂቅ መመሪያ ዙሪያ ውይይት እያደረገ ነው።

የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አቶ መሐመድ እድሪስ፥ ቀደም ሲል በነበሩት የኢትዮጵያ የመገናኛ ብዙሃን ፖሊሲ እና ህጎች መሰረት የሃይማኖት ተቋማት የሃይማኖት ብሮድካስት እንዳያቋቁሙ ህጋዊ እውቅና እና ፈቃድ እንዳያገኙ ተከልክለው መቆየታቸውን አንስተዋል፡፡

በህብረተሰቡ ዘንድ የሃይማኖት መርሃ ግብር በቴሌቪዥን ለመከታተል ከነበረው ፍላጎት ጋር በተያያዘ ሃገራዊ ለውጡን ተከትሎ የሃይማኖት ብሮድካስተሮች በህግ ዕውቅና እንዲያገኙ፤ የመገናኛ ብዙሃን ፖሊሲውም ሆነ የአዋጅ ማሻሻያ በመደረጉ ባለስልጣኑ ፈቃድ አውጥተው እንዲንቀሳቀሱ አስፈላጊውን ሁሉ ያደርጋልም ነው ያሉት ።

በመገናኛ ብዙሃን አዋጅ መሰረትም ከመጋቢት 23 2014 ዓ.ም ጀምሮ ለነባርም ሆነ ለአዳዲስ የሃይማኖት ቴሌቪዥን ፈቃድ አመልካቾች ፈቃድ መስጠት የሚጀምር መሆኑን ተናግረዋል።

በተደረገው ጥናት መሰረት በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ከ50 በላይ የሃይማኖት ቴሌቪዥን ጣቢያዎች በስርጭት ላይ የሚገኙ ሲሆን ፥ ጣቢያዎቹ ሃይማኖታዊ መልዕክቶችን በማስተላለፍ ለተከታዮቻቸው አማራጭ የመገናኛ ዘዴ በመሆን እያገለገሉ እንደሚገኙ ተመላክቷል፡፡

በአንጻሩ ጥቂት የሚባሉ በሃላፊነት ስሜት እና በጥንቃቄ የማይንቀሳቀሱ የሃይማኖት ሚዲያዎች በመኖራቸው በሚያሰራጯቸው መረጃዎች ከህብረተሰቡ የሚደርሱ ቅሬታዎች ከጊዜ ወደ ጊዜ በመጨመር ላይ እንደሚገኙም አንስተዋል።

ከነዚህ ቅሬታዎች ውስጥም ከሕግ፣ ከሞራል፣ ከጤና ጋር የሚቃረኑ ንግግሮችን የማሰራጨት እና ሌሎች ሃይማኖቶችን የመንቀፍ ተጠቃሽ ናቸው ብለዋል።

በመሆኑም የሃይማኖት መገናኛ ብዙሃን ለሃገር አንድነት፣ ለህዝብ መፈቃቀር ፣ አብሮነት፣ መረዳዳት፣ ሰላም እና መሰል በጎ ሃይማንታዊ ዕሴቶችን በማጠናከር የበኩላቸውን ሚና አጠናክረው እንዲቀጥሉ ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።

@Addis_Tv
5.2K views13:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-31 16:38:37
4.2K views13:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-31 16:30:32
የነዳጅ ስርጭት ችግር የሚፈጥሩ የነዳጅ ማደያዎችን እንደማይታገስ የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ አስታወቀ።

ቢሮው በየጊዜው በሚስተዋለው የነዳጅ እጥረት ዙሪያ በከተማው ካሉ የነዳጅ ማደያ ባላቤቶች ጋር የተወያየ ሲሆን በውይይቱ የነዳጅ አቅርቦት ችግር እንዳሌለ ነገር ግን ከስርጭት ጋር ተያይዞ እጥረት መከሰቱ ተገልጿል፡፡

ሆኖም ከስርጭት ጋር ተያይዞ አንዳንድ ማደያዎች የሚፈጥሩትን እንግልትና አሻጥር ፈር ለማስያዝ ጠበቅ ያለ እርምጃ እንደሚወስድና ብልሹ አሰራርን እንደማይታገስ መግለፁን ከአዲስ አበባ ከንቲባ ፅ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

የቢሮው ሃላፊ አቶ አደም ኑሪ ÷ከስርጭት ጋር ተያይዞ በአንዳንድ ማደያዎች የሚፈጠረው ብልሹ አሰራር የምርት ስርጭት ፈተና መሆናቸውን አብራርተው ፤ያልተገባ ጥቅም በመፈለግ እጥረቱን በሚያባብሱ የነዳጅ ማደያዎች ላይ እርምጃ እንደሚወስድ አስረድተዋል።

ችግሩን በዘላቂነት ለመከላከልም የነዳጅ አቅርቦትን በማሳደግ እና ቁጥጥሩን በማጠናከር ሌሊት ነዳጅ በሚሸጡት ላይ የመጠን ማሻሻያ እንደሚደረግና በዘመናዊ የመረጃ ዘዴ ማደያዎች እለታዊ መረጃን ለቢሮው እንዲያሳውቁ ማድረግ የሚያስችል አሰራር የሚዘረጋ መሆኑንም የጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል፡፡

በከተማዋ ከ134 የነዳጅ ማደያዎች 117 ማደያዎች አገልግሎት እየሰጡ የሚገኙ ሲሆን ÷ህገ ወጥ የንግድ እንቅስቃሴ በፈጠሩና በምሽት በበርሜል ነዳጅ ሲሸጡ የተገኙ ሶስት ማደያዎች ላይ ተገቢውን እርምጃ ለመውሰድ መቻሉን አቶ አደም ኑሪ ተናግረዋል፡፡

@Addis_Tv
4.2K views13:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-31 12:00:36
በኢትዮጵያ በአሰላና ኢተያ አካባቢ የ50 ሜጋ ዋት የእንፋሎት ሀይል ማመንጫ ግንባታ ለማከናወን የ100 ሚሊየን ዶላር ስምምነት ተፈረመ።

ስምምነቱን የተፈራረሙት የቱሉ ሞዬ ሀገር በቀል ድርጅትና ሚትስቡሽ ኮርፖሬሽን ሲሆኑ ፕሮጀክቱ የሚከናወነው ከፈረንሳይ መንግስት በተገኘ ፈንድ ነው ተብሏል።

ከእንፋሎት የሚገኝ የሀይል አማራጭ ከአከባቢ ብክለት የፀዳና ዘላቂ በመሆኑ ተፈላጊነቱ ከፍተኛ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን ኢትዮጵያም በዘርፉ እምቅ ሀይል ስላላት ማልማት እንደሚገባ ተመላቷል፡፡

“የእንፋሎት ሀይልን በሀገራችን በስፋት መጠቀም እንፈልጋለን” ያሉት የማዕድን ሚንስትሩ ኢንጂነር ታከለ ኡማ፥ አማራጭ የሀይል ምንጮችን ለማስፋፋት መንግስት ቁርጠኛ ነው ብለዋል።

የበለጸገችና ገናና ሀገር ለመገንባት የሃይል አቅርቦት ወሳኝ መሆኑን ጠቅሰው፥ ለዚህም መንግስት የሚቀጥሉትን 10 አመታት የሚያገለግል ፖሊሲ ቀርፆ ወደ ስራ መግባቱን ተናግረዋል።

ኢንጅነር ታከለ አክለውም በሀይል አቅርቦት ዘርፉ ላይ የግል ዘርፉ እንዲሳተፍ እንደሚፈለግና በዚህም መንግስት ድጋፍ ለማድረግ ቁርጠኛ መሆኑን አስታውቀዋል።

@Addis_Tv
4.1K views09:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-30 15:26:40
በጥቆማ የተያዘ 46 ሺሕ ሊትር ዘይት ለኅብረተሰቡ ሊከፋፈል ነው

በኅብረተሰቡ ጥቆማ በህገወጥ መንገድ በመኪና ተጭኖ የተያዘ ከ46 ሺሕ ሊትር በላይ ዘይት በመሰረታዊ ሸማች አማካኝነት ለኅብረተሰቡ ሊከፋፈል መሆኑ ተገለፀ።

በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 አስተዳደር በመኪና ጥበቃ ላይ በተሰማሩ ነዋሪዎች ጥቆማ ከ2 ሺሕ 300 ካርቶን በላይ ዘይት ጭኖ የነበረ መኪና በኑሮ ውድነትና ገበያ ማረጋጋት ግብረ ኃይል ተወርሶ በወረዳው መሰረታዊ ሸማች ማኅበር አማካኝነት ለኅብረተሰቡ ሊከፋፈል መወሰኑን ወረዳው አስታውቋል።

በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 አስተዳደር ዋና ሥራ አስፈፃሚ ትዝታ ነጋሽ ኅብረተሰቡ መሰል ህገወጥ ተግባራትን ሲመለከት ለሚመለከተው አካል በማሳወቅ የተለመደ ትብብሩን እንዲቀጥል መጠየቃቸውን ከከንቲባ ጽሕፈት ቤት የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡

@Addis_Tv
4.0K views12:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-28 20:56:51
በሀገር ውስጥ የዘረ-መል ምርመራ ከአንድ ወር በኋላ እንደሚጀመር ተገለጸ

በሀገር ውስጥ የዘረ-መል (ዲ ኤን ኤ) ምርመራ ከአንድ ወር በኋላ እንደሚጀመር የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ አስታወቀ።

የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጄነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል እንደገለጹት ፥ አዳዲስ የፎረንሲክ ምርመራ ማሽኖችን ተቋሙ ወደ ሀገር አስገብቶ ጥቅም ላይ እያዋለ ነው።

በአስር ዓመቱ ስትራቴጂክ ዕቅዱ ከአፍሪካ ምርጥ አምስት የፖሊስ ተቋማት አንዱ ሊሆን በለውጥ ላይ የሚገኘው የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ አሰራሮቹን በቴክኖሎጂ እያዘመነ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡

በዚህም ከዚህ ቀደም ወደ ሌላ ሀገራት ተልኮ ይደረግ የነበረው የዲ ኤንኤ ምርመራ ከአንድ ወር በኋላ በኢትዮጵያ ውስጥ ይደረጋል ብለዋል።

ከቴክኖሎጂ ባለፈ ፖሊስ ውጤታማ ስራ ለመስራት ያስችለው ዘንድ አዳዲስ አደረጃጀቶች ማዋቀሩን ኮሚሽነር ጄነራሉ ገልጸዋል።

አዳዲሶቹ አደረጃጀቶች እያደገ የመጣውን የአየር እና የየብስ ትራንስፖርት ደህንነት ለማስጠበቅ የሚያስችሉ ናቸው ተብሎላቸዋል።
ከዚህ በተጨማሪም ኢንዱስትሪዎችንና ዩኒቨርሲቲዎችን ትኩረት አድርገው መዋቀራቸውን አስታውቀዋል።

አዳዲሶቹ አደረጃጀቶች የአቪየሽን ፖሊስ፣ የምድር ባቡር ፖሊስ፣ የዩኒቨርሲቲ ደህንነት ፖሊስ እንዲሁም በኢንዱስትሪ እና ቱሪዝም ላይ ትኩረት አድርጎ የሚከታተል የፖሊስ ክፍሎች ናቸው።

@Addis_Tv
3.8K views17:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ