የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ትናንት የክልሉን አማካሪ ምክር ቤት አቋቁሟል። የአማካሪ ምክር ቤቱ ሚና፣ በክልሉ በሕዝብ የተመረጠ ዲሞክራሲያዊ መንግስት እስኪቋቋም የኅብረተሰቡን ችግሮች፣ ፍላጎቶችና ጥያቄዎች ለጊዜያዊ አስተዳደሩ ማቅረብ እንደኾነ ተገልጧል። ዘጠኝ ተቃዋሚ ፓርቲዎችና ሲቪክ ማኅበራት፣ አማካሪ ምክር ቤቱ ጊዜያዊ አስተዳደሩን የመቆጣጠር ሥልጣን ኖሮት እንዲቋቋም ከትናንት ወዲያ ባወጡት የጋራ መግለጫ ጠይቀው ነበር። @Addis_News 12.9K views07:07