Get Mystery Box with random crypto!

የጠቅላይ ሚኒስትሩ አስገራሚ ንግግር > - ጠ/ሚ ዐብይ አህመድ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን የተና | አዲስ ነገር መረጃ

የጠቅላይ ሚኒስትሩ አስገራሚ ንግግር

<< ኢትዮጵያ ያመጣችውን የኢኮኖሚ ዕድገት ለመገንዘብ ኢትዮጵያውያን 15 ዓመት ያስፈልጋቸዋል >> - ጠ/ሚ ዐብይ አህመድ

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን የተናገሩት < ስለሰው ሰራሽ አስተውሎት ስልጠና ተከታትለው ለተመረቁ ወጣቶች > ህዳር 1 ቀን 2016 ዓ.ም ባስተላለፉት መልዕክት ነው።

ዐብይ እርሳቸው ወደስልጣን ከመጡ በኋላ ያሉት አምስት ዓመታት ከፍተኛ የኢኮኖሚ ዕድገት የተመዘገበበት መሆኑን አስረግጠው ተናግረዋል።

<< ኢትዮጵያ በኢኮኖሚ ዕድገት የዛሬ አምስት አመት ከምስራቅ አፍሪካ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ነበረች >> ሲሉ ያስታወሱት ዐብይ << አሁን ግን አንደኛ አይደለችም >> ሲሉ ተመዝግቧል ያሉትን ዕድገት ማስረዳት ይጀምራሉ።

<< የሁሉም ጎረቤት ሀገራት ዕድገት ተደምሮ፣ ከኢትዮጵያ አንሷል >> ሲሉ ተደምጠዋል። ለዚህ መጥቷል ላሉት ኢኮኖሚያዊ ዕድገት አሐዛዊ መረጃዎች ያልጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን ዕድገት ግን ኢትዮጵያውያን ለመገንዘብ አስርት ዓመታት እንደሚያስፈልጋቸው አስረድተዋል።

ለዚህ ብያኒያቸው < ይሆናል > ያሉትን አመክንዮም አያይዘው አስገንዝበዋል። << እያንዳንዱ ጓዳ ገብቶ፣ የእያንዳንዱ ቤተሰብ ችግር እስኪፈታ ድረስ ሰው ያልደረሰለትን ውጤት በሩቅ አይቶ ሊገነዘብ አይችልም >> ብለዋል።

ዐብይ ከዚህ ቀደምም በብሪክስ ጉባዔ ወቅት ባደረጉት ንግግር ተመሳሳይ ይዘት ያለው መልዕክት ማስተላለፋቸው ይታወሳል።

ዐብይ <<ከግራ ቀኝ የሚሰማው ዜና አንደኛ፣ በዚያ ልክ የሚያውቁ ሰዎች አይደሉም የሚናገሩት፤ኢትዮጵያንም የማያውቁ፣ በትምህርትም ይሄን የሚባል ታሪክ የሌላቸው ዝምብለው የሚተነትኑ ስለሆኑ እነርሱን በመስማት ጊዜ እንዳታባክኑ >>ሲሉ በአደራ ያጀቡትን ማሳሰቢያ ለተመራቂ ወጣቶቹ ነግረዋቸዋል።
Via - አሻም ቴቪ

@Addis_News
@Addis_News