Get Mystery Box with random crypto!

ያሬዳውያን: #ዘቅድስት፡፡ (መዝሙር፤ ምስባክ፣ ምንባባት፣ ወንጌል) #መዝሙር_ዘቅድስት፤ግነዩ ለእ | አቡነ አቢብ (አባ ቡላ)

ያሬዳውያን:
#ዘቅድስት፡፡
(መዝሙር፤ ምስባክ፣ ምንባባት፣ ወንጌል)

#መዝሙር_ዘቅድስት፤ግነዩ ለእግዚአብሔር
ሃሌ ሉያ(፭) ግነዩ ለእግዚአብሔር ወጸውዑ ስሞ፤
ወንግርዎሙ ለአሕዛብ ምግባሮ፤ /መዝ. ፻፬፥፩/
ሀቡ ስብሐተ ለስሙ፡፡ /መዝ. ፷፭፥፪/
አክብሩ ሰንበተ ተገብሩ ጽድቀ፤
ዝግቡ ለክሙ መዝገበ ዘበሰማያት፤
ኀበ ፃፄ ኢያማስኖ ወኢይረክቦ ሠራቂ፤/ማቴ.፮፥፲፱
ድልዋኒክሙ ንበሩ ዘበላዕሉ ሐልዩ፤
ኀበ ሀሎ ክርስቶስ፡፡ /ማቴ. ፳፬፥፵፬/
ትርጕም፤ እግዚአብሔርን አመስግኑ ስሙንም ጥሩ፤ ለአሕዛብም ሥራውን አውሩ፤ ለስሙም ክብር ስጡ፤ ሰንበትን አክብሩ፤ እውነትንም አድርጉ፡፡ ብልና ዝገት በማያጠፉት፣ ሌቦች ቆፍረው በማይሰርቁት ዘንድ ለእናንተ በሰማይ መዝገብ ሰብስቡ፡፡ ክርስቶስ በሚኖርበት ቦታ ያለውን ክብር እያሰባችሁ ተዘጋጅታችሁ ኑሩ፡፡


#እስመ ለዓለም ምሕረቱ
ግነዩ ለእግዚአብሔር ወጸውዑ ስሞ …፤
ግነዩ ለእግዚአብሔር ወጸውዑ ስሞ፤
ነአኵተከ ወንሴብሐከ፤ ለዘዓቀብከነ ወአብጻሕከነ፤
/ግነዩ …/ ወወሀብከነ ጾመ ቅድስተ
ከመ ናግርሮ ለሥጋነ፤
/ግነዩ …/ ወከመ ንትፋቀር በበይናቲነ
ወንኅድግ አበሳ ለቢጽነ፤
/ግነዩ …/ ይእዜኒ እግዚኦ ተራድአነ ሀበነ
ንትቀነይ ለከ ለነ፤ ለአግብርቲከ ወለአዕማቲከ፤
/ግነዩ …/ አብ ቀደሳ ወአልዓላ ለዕለተ ሰንበት፤
/ግነዩ …/ ኅብስተ እምሰማይ ፈኖከ ሎሙ
ከመ ይብልዑ ወይጽገቡ፤
/ግነዩ …/ በ፪ኤ ዓሣ ወበ፭ቱ ኅብስት
አጽገቦሙ ኢየሱስ ለ፶፻ት፤
/ግነዩ …/ ወሠርዓ ሰንበተ ለሰብእ ዕረፍተ
ውብውህ ሎቱ ይኅድግ ኃጢአተ፤
ግነዩ ለእግዚአብሔር ወጸውዑ ስሞ ወንግርዎሙ ለአሕዛብ ምግባሮ፨

#አራራይ፤
ሃሌ ሉያ፤ ለክርስቶስ ይደሉ ስብሐት፤
ለዘአብጽሐነ እስከ ዛቲ ሰዓት፤
እግዚአ ለሰንበት ዘልማዱ ኂሩት፤
ሎቱ ስብሐት ለዘቀደሳ ለሰንበት፡፡

#ዕዝል፤
በወንጌል ኮነ ሕይወትነ፤
ሃሌ ሉያ(3)፤
ሰንበት ቅድስት ለውሉደ ሰብእ መድኀኒት፤
ለሙታን መንሥኢ፡፡

#ሰላም፤
ሰንበት ይእቲ ቅድስት ይእቲ፤
ሰንበት ተዓቢ እምኵሉ ዕለት እስመ ሰንበትሰ በእንተ ሰብእ ተፈጥረት፤
ሰንበተ ሰንበታቲሁ ለውሉደ ሰብእ መድኀኒት፤
ጽዮን ቅድስት ሰላማዊት፤
ታስተርኢ እምርኁቅ ከመ ማኅቶት፡፡
#ምንባባት
፩ኛ.ተሰ ፬÷፩-፲፫፤ እግዚአብሔርን ደስ ልታሰኙ እንደሚገባችሁ እንመክራችኋለን፡፡/ቊ.1
፩ኛ.ጴጥ.፩÷፲፫፤ ኢየሱስ ክርስቶስ ሲገለጽ የምታገኙትን ጸጋ ፈጽማችሁ ተስፋ አድርጉ፡፡ /ቊ.13/
የሐዋ. ሥራ ፲፥፲፯-፴፤እግዚአብሔር ማንንም ሰው ርኵስና የሚያፀይፍ ነው እንዳልል አሳየኝ፡፡ /ቊ.28/
#ምስባክ፤ መዝ. ፺፭÷፭
እግዚአብሔርሰ ሰማያት ገብረ፤
አሚነ ወሠናይት ቅድሜሁ፤
ቅዳሳት ወዕበየ ስብሐት ውስተ መቅደሱ፡፡

(ትርጕም፤እግዚአብሔር ግን ሰማያትን ፈጠረ፤ እምነትና በጎ ምግባርም በፊቱ ነው፤ ቅድሳትና የምስጋና ገናናነትም በመቅደሱ ውስጥ ናቸው፡፡)
#ወንጌል፤
ማቴ. ፮÷፲፮-፳፭፤
ሌቦች ቆፍረው በማይሰርቁት ዘንድ ለእናንተ በሰማይ መዝገብ ሰብስቡ፡፡ /ቊ. ፳/)
#ቅዳሴ፤
ቅዳሴ ዘኤጲፋንዮስ

መዝሙር ዘቅድስት
በ (፭/ር) ግነዩ ለእግዚአብሔር ወጸውዑ ስሞ ወንግርዎሙ ለአሕዛብ ምግባሮ ሀቡ ስብሐተ ለስሙ አክብሩ ሰንበተ ተገበሩ ጽድቀ ዝግቡ ለክሙ መዝገበ ዘበሰማያት ኀበ ፃፄ ኢያማስኖ ወኢይረክቦ ሰራቂ ድልዋኒክሙ ንበሩ ዘበላዕሉ ሀልዩ ኀበ ሀሎ ክርስቶስ።

ትርጉም፦

ለእግዚአብሔር ተገዙ ስሙንም ጥሩ ሥራውን ለአሕዛብ ንገሯቸው ለስሙ ምስጋናን ስጡ/አቅርቡ ሰንበትን አክብሩ ጽድቅን ሥሩ ሌባ በማያገኘው ብል በማያጠፋው በሰማያት መዝገብን አከማቹ ክርስቶስ ባለበት ለመሆን በላይ ያለውን እያሰባችሁ ተዘጋጅታችሁ ኑሩ።

የዕለቱ ምስባክ፦

እግዚአብሔርሰ ሰማያተ ገብረ፤
አሚን ወሠናይት ቅድሜሁ፤
ቅድሳት ወዕበየ ስብሐት ውስተ መቅደሱ። መዝ ፺፭፥፭

ትርጉም፦

እግዚአብሔር ግን ሰማያትን ፈጠረ፤
እምነትና በጎነት በፊቱ ናቸው፤
ቅድስና እና የክብር ገናንነት በመቅደሱ ውስጥ ናቸው።

ምሥጢር፦

እግዚአብሔር ሰባቱን ሰማያት ፈጠረ፤
ሃይማኖት ምግባር በፊቱ ነው አለ ምግባር ሃይማኖት የያዘ ሰውን ይወዳል፤
ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ ተብሎ መመስገን ዓቢየ ስብሐት መባል ገንዘቡ ነው።n

መልእክት፦

ሰማይ ማለት ሥዕለ ማይ - የውኃ ንድፍ ማለት ነው አንድም ልዑል ማለት ነው። ቀለሙ/መልኩ ሰማያዊ ነው እጅግ ብሩህ ቢሆን ዐይን ይበዘብዝ ነበርና እጅግም ጨለማ ቢሆን ለዐይን ይከብድ ነበርና። ይህንንም የፈጠረው የዐይን ማረፊያ ይሆን ዘንድ ነው ጠፈር/ሰማይ ባይኖር የሰው የእንስሳ የአራዊት ዐይን ሁሉ ማረፊያ አጥቶ ወልቆ ወልቆ በወደቀ ነበርና።
ይህ ለሥጋዊ እንቅስቃሴአችን ሲሆን ለመንፈሳዊው እንቅስቃሴያችን ደግሞ በተለይ በጊዜ ቅዳሴ የዐይናችን ማረፊያ የሚሆነው ቅዱስ ሥጋውና ክቡር ደሙ ነው። አምላክችን ምግባር ከሃይማኖት አንድ አድርጎ የያዘ ሰውን ይወዳል ባልነው መሠረት አስቀድሳለሁ ብሎ ከቤቱ ተዘጋጅቶ ወደ ቤተ ክርስቲያን የሚመጣ ሰው በዕለቱ የታወቀና ድንገተኛ ነገር ካላጋጠመው በስተቀር ሥጋ ወደሙን ይቀበል ዘንድ ወዶና ፈቅዶ የሚኖርበት ክርስቲያናዊው ሕግ ያስገድደዋል ይህን ካላደረገ ዐይኑ ማረፊያ ያጣ ሰው ሆኗል።
“እግዚአብሔርሰ ሰማያተ ገብረ - እግዚአብሔርማ ሰማያትን ፈጠረ” ብሎ ለመዘመር አቅም የሚያንሰው ይሆናል። ዐይናችን ማረፊያ ሲያገኝ ልባችንም በተስፋ የተመላ ይሆናል እንዲህ ከሆነ ዐይን ያላያትን በሰው ልብ ያልታሰበችውን እግዚአብሔር ለወዳጆቹ ያዘጋጃትን ዘለዓለማዊት መንግሥት በተስፋ እየጠበቀ የመኖር ዕድሉ ከቀን ወደቀን ያድጋል “ትምጻእ መንግሥትከ - መንግሥትህ ትምጣልን” እያለ ይጸልያልና።


 የዐቢይ ጾም ስለሁለቱ ሳምንታት ዘወረደ እና ቅድስት



@mekra_abaw



@firehaymanotgroup



@ABUNE_ABIB