2023-04-20 22:25:10
ከዒድ ጠዎት ጀምሮ መፈፀም ያለብን
▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬ ▬
ከዒድ ጠዎት ጀምሮ መፈፀም ያለብን ነገሮች:-
①) መታጠብ እራስን ማሰማመር እና ከልብሶች መካከል የተሸለውን እና ቆንጆውን መልበስ፣
:
②) ወደ መስገጃው ከመውጣታችን በፊት ቴምር መብላት (አንድ፤ ሶስት፤ አምስት…) ማለትም
ኢ-ተጋማሽ ቁጥር ያላቸውን ተምሮች በልቶ መውጣት፣
:
③) ዒድ መሆኑ ከተረጋገጠበት ሰዐት አንስቶ ሰላቱ እስኪጀመር ተክቢራ ማለት፣
:
④) ለኢድ ሰላት ከመውጣት በፊት ዘካተል-ፊጥርን ለተገቢው ወገን መስጠት፣
:
⑤) ሰላቱ ከተጠናቀቀ በኋላ በተቻለ አቅም ኹጥባን ማዳመጥ (ይሁን እንጅ ኹጥባን ማዳመጥ ግዴታ አይደለም)፣
:
⑥) ወደ ዒድ ሰላት ከሄዱበት መንገድ በሌላ መንገድ ቀይሮ መመለስ፣
:
⑦)የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት መለዋወጥ፣ እንኳን አደረሳችሁ ስትባሉ «ተቀበለላሁ ሚና ወሚንኩም ሷሊሃል አዕማል» ብሎ መመለስ የተለያዩ የኢስላም ሊቃውንት ከሰሃቦች መገኘቱን አረጋግጠዋል፡፡
*
ሚያዚያ 12, 2015 E.C
አቡ ሒባ
||
የቴሌግራም ቻናል:-
t.me/AbuHiba
449 viewsYasin Muhammed - አቡ ሒባ, edited 19:25