"ጉንዳኖች" የአሏህ ፉጡሮች ናቸውና አሏህን ስለሚያወሱ፣ እቤት ወሥጥ ካላስቸገሩ ሊገደሉ አይገባም። እምግብ ላይና እቃ ላይ እየገቡ የሚያስቸግሩ ከሆነ ከቤት እንድታስወግዱት እንመክራለን። እንደዚህ ያለው"ጉንዳን" ‹ጂን› ሊሆን ስለሚችል አያት -ል- ኩርሲይንና ሙዓዊዛቶችን (ከጂን የመጠበቂያ ቁርኣናዊ አንቀፆች) ቢቀሩበት መልካም ነው። እቤቱ ውሥጥ በጉንዳን የተቸገረ፣ ታማኝ ጓደኛዬ የሚከተለውን በማለት አጫውቶኛል፦ ‹ ቤታችን በጉንዳን ተወሮ ነበር ፣ ቁርኣን ስንቀራበት ለአንድ ሳዓት ያክልጂ ምንም እቤታችን አልተቀመጠም። ከቤታችን ሙሉ ለሙሉ ሙልጭ ብሎ ነው የወጣው። › ቁርኣን ተቀርቶበት ካልወጣ ፣ ትንሽ ግዜ ጠብቆ ከእሳት ውጭ ባለ ነገር፣ በጉንዳን ማጥፊያ መድሃኒቶች መግደል ይቻላል። ግን በእሳት መግደል አይቻልም!። الشيخ سليمان الرحيلي አብደረህማን አማን t.me/abdu_rheman_aman 279 viewsلَتَرْكَبُنّ طَبَقاً عَنْ طَبَق, edited 04:24