Get Mystery Box with random crypto!

ሰላተል ኩሱፍ ( የፀሀይ ግርዶሽ ሰላት ) ፀሀይ በጨረቃ ግርዶሽነት ምክንያት ብርሀኗ ከመሬ | Aß Mustefa

ሰላተል ኩሱፍ ( የፀሀይ ግርዶሽ ሰላት )

ፀሀይ በጨረቃ ግርዶሽነት ምክንያት ብርሀኗ ከመሬት ሲጋረድ የሚሰገደው ሱና የሆነው ሰላት (ሰላት ኩሱፍ) (صلاة الكسوف) ይባላል ። ጨረቃ ደሞ በመሬት አማካኝነት ስትጋረድ የሚሰገደው ሰላት (ሰላተል ኹሱፍ) (صلاة الخسوف ) ይባላል።

የፀሀይ ኩሱፍ ሰላት በሸሪዐ የተደነገገው በሁለተኛው አመተ ሂጅራ ሲሆን ፤ የጨረቃ ኹሱፍ ሰላት ደሞ በአምስተኛው አመተ ሂጅራ ነው። (ሁለቱም ሰላቶች ሱና ናቸው ለወንድም ለሴትም ። በጀመዐ መስገዱ የተወደደ ቢሆንም ለብቻም መስገድ ይቻላል። )

አሰጋገዱ
ሁለት አይነት አሰጋገድ አለው

አንደኛው - ሁለት ረክዐ እንደማንኛው ረክዐተይን ሰላት ። ኡሰሊ ሱነተ ሰላተል ኩሱፍ ብሎ መስገድ ይቻላል።

ሁለተኛው - በሁለት ቂያምና በሁለት ሩኩዕ ይሰገዳል ።
- ነይቶ በተክቢር ወደ ሰላት ይገባል። መክፈቻ ዱዐውን ይላል
- ፋቲሀና ሱራ ይቀራል ( ረጅም ሱራ ቢሆን ይመረጣል )
- ሩኩዕ ይወርዳል
- ከሩኩዕ ይነሳል፤ ረበና ለከል ሀምድ ብሎ ዱዐውን ይላል
- ከዛ ድጋሚ ፋቲሀና ሱራ ይቀራል ( ከመጀመርያው ሱራ አነስ ያለ ቢሆን ይመረጣል )
- ሩኩዕ ይወርዳል
- ከሩኩዕ ይነሳል
- ረበና ለከል ሀምድ ብሎ የኢዕቲዳል ዱዐ ይላል
- ሱጁድ ይወርዳል ፤ ይነሳል፤ ሁለተኛ ሱጁድ ያደርጋል
- ከዛ ተነስቶ ሁለተኛውንም ረክዐ በእንደዚህ አይነት ይጨርሳል።

በሁለተኛው አሰጋገድ ላይ አምልጦት የመጣ ረክዐዋን ለማግኘት የመጀመርያዋን ሩኩዕ ማግኘት አለበት ። ከአንዱ ረክዐ የመጀመርያው ሩኩዕ ያመለጠው ረክዐው አምልጦታል።

ከሰላት ቡሀላ እንደ ጁምዐ አይነት ሁለት ኹጥባ ማድረግ ይወደዳል።

የሰላቱ ግዜ የሚወጣው .. የፀሀዩ ግርዶሽ ሙሉ በሙሉ ሲወገድ ወይም ደሞ ምሽት ደርሶ ፀሀይዋ ስትጠልቅ ነው
የጨረቃውም ግርዶሹ ሙሉ ለሙሉ ከተወገደ ወይም ደሞ ነግቶ ፀሀይ ከወጣች ጊዜው ይወጣል።

ሰይዳችን ሰ.ዐ.ወ. ከስር የተጠቀሰው ሀዲሳቸው ላይ : '' ፀሀይና ጨረቃ ሁለቱ ከአላህ ተዐምራቶች ውስጥ ናቸው። ለማንም መሞት ወይም መኖር አይደለም የሚጋረዱት። ይሀንን ካያቹ ወደ ሰላት ሽሹ '' ብለዋል።

عن عائشة زوج النبي صلى الله عليه وسلم قالت : خسفت الشمس في حياة رسول الله صلى الله عليه وسلم فخرج رسول الله صلى الله عليه وسلم إلى المسجد فقام وكبر وصف الناس وراءه فاقترأ رسول الله صلى الله عليه وسلم قراءة طويلة ثم كبر فركع ركوعا طويلا ثم رفع رأسه فقال سمع الله لمن حمده ربنا ولك الحمد ثم قام فاقترأ قراءة طويلة هي أدنى من القراءة الأولى ثم كبر فركع ركوعا طويلا هو أدنى من الركوع الأول ثم قال سمع الله لمن حمده ربنا ولك الحمد ثم سجد ثم فعل في الركعة الأخرى مثل ذلك حتى استكمل أربع ركعات وأربع سجدات وانجلت الشمس قبل أن ينصرف ثم قام فخطب الناس فأثنى على الله بما هو أهله ثم قال إن الشمس والقمر آيتان من آيات الله لا يخسفان لموت أحد ولا لحياته فإذا رأيتموها فافزعوا للصلاة }

رواه مسلم

@elmeewa
@Ab_Mustefa