Get Mystery Box with random crypto!

በነቢዩ (ዐሰወ) ዘመን አንዲት በጌጣጌጥ የተሸለመች ሴት በመንገድ ስትሄድ አይሁዳዊ ያገኛትና ለወር | Aß Mustefa

በነቢዩ (ዐሰወ) ዘመን አንዲት በጌጣጌጥ የተሸለመች ሴት በመንገድ ስትሄድ አይሁዳዊ ያገኛትና ለወርቋ ሲል ጭንቅላቷን በድንጋይ መትቶ ገደላት። ነቢዩም (ዐሰወ) የሴቲቱ ነፍስ ልትወጣ ስትቃረብ ደረሱባትና ማን እንደመታት ይጠይቋት ጀመር። «እገሌ ነው?» አሏት። «አይደለም» በማለት በምልክት ነገረቻቸው። ሌላም ሰው ጠሩ። «አይደለም» አለች። በመጨረሻ የአይሁዳዊውን ስም ጠሩላት። «አወ!» አለቻቸው። ከዚያም ነፍሷ ወጣች።

ነቢዩም (ዐሰወ) አይሁዳዊውን አስመጥተው ጥያቄዎችን ጠየቁት። እሱም ወንጀሉን መፈፀሙን ተናዘዘ። ከዚያም ሴቲቱን በገደላት መልኩ እንዲገደል አዘዙ። በድንጋይ ተወግሮም ተገደለ።
(አንነሳዒ 4742)

የሴቶች መብት ነቢዩ (ዐሰወ) ከሄዱበት መንገድ ውጭ ሊከበር አይችልም።

@Ab_Mustefa