Get Mystery Box with random crypto!

የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን

የቴሌግራም ቻናል አርማ aaeqocaa — የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን
የቴሌግራም ቻናል አርማ aaeqocaa — የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን
የሰርጥ አድራሻ: @aaeqocaa
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.80K
የሰርጥ መግለጫ

https://www.facebook.com/AA-Educational-Training-Quality-Occ-Competency-Assurance-Authority-100864428091362/?__tn__=-UC*F

Ratings & Reviews

1.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-08-17 15:41:52 11/12/2014
የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ለአጫጭር የቴክኒክና ሙያ ማሠልጠኛ ተቋማት በስታንዳርድ የኢንስፔክሽን ቼክ ሊስት ላይ ግንዛቤ ሠጠ።

የትምህርት ስልጠና ጥራት ማረጋገጥና ምርምር ዳይሬክቶሬት በባለስልጣኑ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ላይ ባካሄደው የግንዛቤ መስጫ መድረክ ላይ የት/ስ/ጥ/ማረጋገጥና ምርምር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ ገነት ኃ/የሱስ ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለጹት
ዳይሬክቶሬቱ በአለም አቀፍ እና በአገር አቀፍ ያለውን ተሞክሮ በመቀመር የኤንስፔክሽን ቼክሊስት በማዘጋጀት እና ግንዛቤ በመስጠት በ2014 ዓ.ም ወደ ምዘና መግባቱን አስታውሰው ሆኖም ኤንስፔክሽን ስራው ከተከናወነ በኃላ እስታንዳርዱ እና ተቋማቱ ያሉበት ሁኔታ መራራቁን መገንዘባቸውን ተናግረዋል፡፡

በዚህም ከተማ አቀፍ ነባራዊ ሁኔታ ያገናዘበ ቼክሊስት ማዘጋጀት በማስፈለጉ ከዚህ ቀደም በተቋማቱ የተሰጡትን አሳቦች እና ያሉበትን ሁኔታ ግንዛቤ ውስጥ በመክተት ቼክሊስቱ ላይ ማስተካከያ በማድረግ  ተዘጋጅቷል ፡፡
የቴክኒክና ሙያ ማሠልጠኛ ተቋማት በአገር ደረጃ የሥራ እድል ከመፍጠር አኳያ ያላቸውን አስተዋጽኦ ግንዛቤ ውስጥ በማስገባት መሠራቱንም ጨምረው ገልጸዋል፡፡
በነዚህ ማሠልጠኛ ተቋማት የሚያልፍ ሠልጣኞች ብቁ የሆኑ ጥራቱን የጠበቀ ስልጠና እንዲያገኙ ለማድረግ ጥራቱን የማረጋገጥ ኃላፊነቱን የወሰደው ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በመሆኑ ይህንን መሠረት በማድረግ ቼክ ሊስት የተዘጋጀ ሲሆን ተቋማቱ ወደ ስታንዳርዱ እንዲመጡ ለማስቻል ጥረት ተደርጎል ብለዋል ፡፡ 
ተቋማቱ በቂ ግንዛቤ በመውሰድ ጥራት ያለው ስልጠና በመስጠት የተሻላ ውጤት ማስመዝገብ እንደሚገባቸው አስገንዝበዋል፡፡
በዕለቱ ኢንስፔክሽን ቼክ ሊስት ሰነድ በአቃቂ ቃሊቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ስራ አስኪያጅ በአቶ አብርሃም ምትኩ ቀርቧል
ባሳለፍነው በጀት አመት የእስታንዳርድ ኤንስፔክሽን ተደርጎ ተቋማቱ የት ላይ እንዳሉ ለመረዳት መቻሉን ጠቅሰው የትምህርት ስልጠና ጥራት በአንድ አካል ብቻ ስለማይረጋገጥ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ኃላፊነታቸውን ሊወጡ እንደሚገባ አስገንዝበዋል
በቀረበው ሰነድ ላይ ጥያቄና አስተያየት የተሰጠ ሲሆን በግንዛቤ መስጫ መድረኩ ላይ ከ150 በላይ የሚሆኑ ተቋማት በውይይቱ ላይ መሳተፋቸው ታውቋል ፡፡

#ነጻ የጥቆማ የስልክ መስመር 9302
የባለስልጣኑ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት
493 views12:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-17 15:41:51
598 views12:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-16 19:19:13 10/12/2014
በቀጣይ የሚተገበረው አዲሱ ስርዓተ ትምህርት በሚጠበቀው የጥራት ደረጃ መተግበር እንደሚገባ ተገለጸ።

የትምህርት ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን እና የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ በጋራ በመሆን በስርዓተ ትምህርት ትግበራ ዙሪያ ከግል የት/ቤት ተቋማት ጋር ውይይት አድርገዋል፡፡ 

በውይይት መድረኩ ላይ የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ አድማሱ ደቻሳ ባስተላለፉት መልዕክት እንደገለጹት
የስርዓተ ትምህርት ትግበራው ለዜጎች ሁለንተናዊ እድገት የሚያስፈልጉ የትምህርት ጥራትን መሠረት አድርገው የሚሠጡ እንዲሆን በተለያዩ የትምህርት አደረጃጀት የሚሠጥ መሆኑን ጠቅሰው ባለፈው የትምህርት ዘመን የትምህርት ትግበራው የተገኙ መልካም ውጤቶች እንዳሉ ሁሉ በትግበራ ሂደት የነበሩ ክፍተቶች በቀጣይ መስተካከል ያለባቸው ጉዳዩች መኖራቸውን አሳውቀዋል፡፡
በ2015 የትምህርት ዘመን የሚተገበረው ሁለት አይነት የስርዓተ ትምህርት አይነት ሆኖ ነባሩ ስርዓተ ትምህርት የሚቀጥልባቸው ሲኖሩ አዲሱ ስርዓተ ትምህርት ወደ ሙሉ ትግበራ የሚገባባቸው የትምህርት ደረጃዎች መኖራቸውን ተናግረዋል፡፡

በትግበራ ሂደቱም በአንደኛው ምዕራፍ አንደኛ ደረጃ በመካከለኛ ደረጃ የሙከራ ትግበራ በ2014ዓ.ም የተከናወነበት እና በ2015 ወደ ሙሉ ትግበራ የሚገባበት ሲሆን በቅድመ አንደኛ እና በአጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ እንዲሁም በተወሰኑ ትምህርት ቤቶች ላይ የሙከራ ትግበራ የሚደረግ እና በ2016 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ወደ ሙሉ ትግበራ የሚገባ ይሆናል
በአገር አቀፍ የተሰራውን ስርዓተ ትምህርት ሪፎርም ወደ ከተማው በማምጣት የማስማማት ስራ እየተሰራ ሲሆን ትምህርቱ በሚሰጥባቸው ቋንቋዎች ወደ አማርኛ እና አፋን ኦሮሞ የመተርጎም የስርዓተ ትምህርት የማስተማሪያ መፅሐፍ እና የመምህር መምሪያ ማዘጋጀት ስራ በመስራት የመፅሐፍ ህትመት ላይ እንደሚገኝ አሳውቀዋል
በዕለቱ የትምህርት ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ምክትል ስራ አስኪያጅ በሆኑት በወ/ሮ ፍቅርተ አበራ በግል የትምህርት ተቋማት የስርዓተ ትምህርት አተገባበር ያለበት ሁኔታ በተመለከተ ሰነድ ቀርቧል፡፡በሰነዱ ላይም በተቋማቱ ላይ የሚታየውን የስርዓተ ትምህርት ክፍተት ተዳሶል
ዜጎች የተሻለ ደረጃ እንዲደርሱ ስርዓተ ትምህርት በጋራ እኩል መተግበር ያለበት ሲሆን ጥራት ያለውን ትምህርት ለዜጎች ለማድረስ ለሁሉም የባለድርሻ አካላት የጋራ ጥረት መኖር እንዳለበት ወ/ሮ ፍቅርተ አስገንዝበዋል ፡፡
በተጨማሪም በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት ሪፎርም  በተመለከተ በትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ በአቶ አድማሱ ደቻሳ ሰነድ ቀርቧል፡፡ በቀረቡት ሰነዶች ላይ በተሰታፊዎች ጥያቄና አስተያየት ቀርቧ ውይይት ተደርጎበታል
በውይይት መድረኩ ላይ ከትምህርት ስልጠና ቁጥጥር ባለስልጣን እና ከአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ የተውጣጡ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች እንዲሁም ጉዳዩ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተሳታፊ ሆነዋል፡፡

#ነጻ የጥቆማ የስልክ መስመር 9302
የባለስልጣኑ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት
"ከኮሮና ቫይረስ ራስዎንና ሌሎችን ይጠብቁ"
478 views16:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-16 19:19:12
442 views16:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-16 10:41:54
10/12/2014

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር  ትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን እና ት/ ቢሮ በጋራ በመሆን በ2015 ዓ.ም የስረዓተ ት/ት ትግበራ ዙሪያ ከግል ት/ቤት ተቋማት ጋር  ውይይት እያከናወኑ ነው።

#ነጻ የጥቆማ የስልክ መስመር 9302
የባለስልጣኑ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት
"ከኮሮና ቫይረስ ራስዎንና ሌሎችን ይጠብቁ"
610 views07:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ