Get Mystery Box with random crypto!

በእውነት ስለ እውነት

የቴሌግራም ቻናል አርማ zdagimm —   በእውነት ስለ እውነት
የቴሌግራም ቻናል አርማ zdagimm —   በእውነት ስለ እውነት
የሰርጥ አድራሻ: @zdagimm
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 400
የሰርጥ መግለጫ

✞እዉነትን ለማግኘት በእውነት መጓዝ ግድ ነው✞


✝የአባቶችን ትምህርትም እናስተምራለን ተስፋቸውንም ተስፋ እናደርጋለን የምናምንባት የተማርናት ተስፋ የምናደርጋት ሃይማኖት ይህች ናት እንኖርባታለን እንሞትባታለን በእግዚአብሔር ፈቃድ እንነሣባታለን
ሃይማኖተ አበው ዘአባ ገብርኤል ፺፬:፳፪
☝☝☝☝☝☝☝☝☝

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-05-29 16:57:12
112 views13:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-11 11:03:37 + ወርቃማዎቹ አባቶቻችን እንዲህ አሉ +

"ሰዎች የሚያብዱበትና እንደነሱ ያላበደ ሰው ሲያዩ "እንደኛ ስላልሆንክ አብደሃል" የሚሉበት ዘመን ይመጣል"
ቅዱስ እንጦንዮስ

. . . . .

"እግዚአብሔርን ከግርማው ታላቅ የተነሣ ብቻ አትፍራው:: ከፍቅሩ ታላቅነት የተነሣ ፍራው"
ቅዱስ ይስሐቅ ሶርያዊ

. . . . .

"የጥበብ መጀመሪያው እግዚአብሔርን መፍራት ነው:: የጥበብ መጨረሻው እግዚአብሔርን ማፍቀር ነው:: የመጨረሻው ደረጃ ላይ ስትደርስ እግዚአብሔርን ከመፍራት ወደ ፍጹም ፍቅር ትደርሳለህ:: ፍቅር ፍጹም ፍርሃትን አውጥቶ ይጥላልና" ቅዱስ እንጦንዮስ ዘየዓቢ

. . . . .

"ለልጆችህ ስለ እግዚአብሔር ከምትነግራቸው የበለጠ ለእግዚአብሔር ስለ ልጆችህ ንገረው"
አባ ኤጲፋንዮስ ዘአቴና

. . . . .

"እውነተኛ እውቀት የትሕትና ፏፏቴ ነው"
ቅዱስ ይስሐቅ ሶርያዊ

. . . . .

"ጌታ ጴጥሮስን በባሕር ላይ ሊወድቅ ሲል በሚታይ እጁ የያዘው በየብስ ላይ በማይታይ እጁ እንደያዘው ለማስተማር ነበር" ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ

. . . . .

"ክርስትና እጅግ ኃያል የሚሆነው በዓለም በተጠላ መጠን ነው" ቅዱስ አግናጥዮስ

. . . . .

"ይህንን ካስታወስክ በሰው መፍረድ ታቆማለህ:: ይሁዳ ሐዋርያ ነበር:: ከጌታ ቀኝ የተሰቀለው ወንበዴ ነፍሰ ገዳይ ነበር" ቅዱስ ዮሐንስ ዘሰዋስው
159 views08:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-09 17:55:42 ግንቦት ፩ ልደታ ለማርያም

ልደቱ የኛ ወይስ የአንቺ?

ባንቺ ልደት... መርገሙ ከራቀ
በደል ከወደቀ
ጌታ ከወረደ
ሳጥናኤል ከራደ

ባንቺ ልደት....ዓመተ ፍዳ ተፈጽሞ
ምህረት ተሹሞ
ጌታ ከሰማይ ሊወርድ
ከኛ በስጋ ሊዛመድ

ባንቺ ልደት..የሀዘናችን ሰንሰለት..በሀዲስ ኪዳን ስትፈቺ
እመቤቴ ይኸ ልደትሽ...የኛ ልደት ነው ...ወይስ የአንቺ?

ስለዚህ እመቤታችን....

ልደትሽ ....ልደታችን ነው፡፡
አንቺ የወጣሽው...ከማህጸን ነው
እኛ ግን .....ከጨለማ ነው
ይኸውም...በልደትሽ ነው፡፡

#ሰአሊለነ_ቅድስት

እንኳ አደረሳችሁ!!!
ይህ ቀን የእመቤታችን ሳይሆን የዓለሙ ሁሉ ልደት ነው፡፡
224 views14:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-09 12:38:06
111 views09:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-24 04:26:40 "…እንግዲህ ክርስቶስ በአብ ክብር ከሙታን እንደ ተነሣ እንዲሁ እኛም በአዲስ ሕይወት እንድንመላለስ፥ ከሞቱ ጋር አንድ እንሆን ዘንድ በጥምቀት ከእርሱ ጋር ተቀበርን። ሞቱንም በሚመስል ሞት ከእርሱ ጋር ከተባበርን ትንሣኤውን በሚመስል ትንሣኤ ደግሞ ከእርሱ ጋር እንተባበራለን" ሮሜ 6፥ 4-5
191 views01:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-24 04:18:50 ከመጀመሪያው ጥፋት ተጠያቂነት ሁላችንን ነጻ ያደርገን ዘንድ መቅደስ ሰውነቱን ስለ ሁላችን ሲል ለሞት አሳልፎ ሰጠ ፡፡"
ቅዱስ አትናቴዎስ
178 viewsedited  01:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-19 21:39:52
ሕዝቡ {በርባን ይፈታልን ክርስቶስ ግን ይሰቀል }ማለታቸውን ስንሰማ ሁላችንም ማዘናችንና <ምን አይነት ክፉዎች ናቸው }ብለን መውቀሳችን አይቀርም ። ወዳጄ ሆይ እባክህን እሰኪ አይሁድንና ጲላጦስን ለአፍታ እንተዋቸው! አንተ ብትሆን ኖሮ ከጌታና ከበርባን ማናቸውን ትፈታለህ? የእስክንድርያ ትምህርትቤት መምህር የነበረው ሊቅ <<በስጋው ክፉ ነገርን የሚሠራ ሁሉ በርባንን ፈቶ ክርስቶስን አሰረው ።መልካም ነገርን የሚያደርግ ደግሞ ክርስቶስን ፈቶ በርባንን አስሮታ ልይላል ።}} ወዳጄ ሆይ አንተ በሰውነትህ ላይ ፈተህ የለቀከው ማንን ነው ?በርባንን ነው ወይስ ጌታን ነው ?በርባንን ፈተኸው ከሆነ ዛሬውኑ በንስሃ ተመልሰህ ፈጣሪህን በሰውነትህ ውስጥ አክብረው ።<በርባንን የፈታሁት እኮ ወድጄ አይደለም ሁኔታዎች አስገድደውኝ ነው >ብለህ እንደ ጲላጦስ ለራስህ ይቅርታ ማድረግ ና እጅህን መታጠብ አይበጅህም ። ይልቅስ አሁኑኑ ጌታህን ፈተኽ በርባን የተባለ ኃጢአትን ስቀለው ያን ጊዜ የክርስቶስ መሆንህ ይታወቃል ።!
{የክርስቶስ ኢየሱስ የሆኑት ስጋን ከክፉ መሻቱና ምኞቱ ጋር ሰቀሉት }}ተብሎ ተጽፏልና (ገላ 5፥24)

#ሕማማት
186 views18:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-09 06:37:08 ደረሰው፡፡ እኛ ሰው ሆኖ ያየነውን እግዚአብሔርን አየው፡፡ (ዘጸ.33፡18-23፤ማቴ.17፡3፤ዮሐ.1፡14) እግዚአብሔር ከመቃብር ቀስቅሶ ለጸሎት ምላሽ የሚሠጥ ከሆነ ለዘካርያስ በእስተርጅናው መልስ ቢሠጠው ምን ያስደንቃል?

እዚህ ላይ አንድ ጥያቄ እናንሣ፡፡ እግዚአብሔር ለካህኑ ዘካርያስና ለሚስቱ ኤልሳቤጥ ልጅ መሥጠቱ ካልቀረ ለምን ወዲያው አልሠጣቸውም? ‹ልጅ በልጅነት ነው› እንደሚሉት ብሂል በልጅ አምሮት በተሰቃዩበት እና በደስታ ሊያሳድጉ በሚችሉበት ጊዜ ልጅ መስጠት እየቻለ አምሮታቸው ከጠፋና ተስፋ ከቆረጡ በኋላ መሥጠቱ ለምንድን ነው? ሽማግሌው ዘካርያስ ልጁን ሮጦ በማያጫውትበት ፣ እንደልቡ በማያዝልበት ፣ ወደ ቤተ መቅደስም ወስዶ በሙሉ ጉልበቱ ሥርዓቱን ለልጁ በማያስተምርበት በእርጅና ዘመኑ ፈጣሪ አምጥቶ ልጅ መሥጠቱ ለምን ይሆን? አንዳንድ ሰው እንደሚለው ‹ፈጣሪ ካላጣው ጊዜ› ምነው ቀደም አድርጎ ቢሰጣቸው? አይችልም ነበር?

ይችላል! ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለም፡፡ ወጣት እያሉ ልጅ ሊሠጣቸው ይችላል፡፡ ያዘገየው ግን በሌላ ምክንያት ነው፡፡ እነዚህ ባልና ሚስት በወጣትነታቸው ቢወልዱ ኖሮ ልጅ አግኝተው ይደሰቱ ነበር፡፡ ዘካርያስም በእግሩ የሚተካ ካህን ያገኝ ነበር፡፡ እግዚአብሔር ግን ለእነዚህ በሕጉና በትእዛዙ ለሔዱ በፊቱ ጻድቃን ሆነው ለተገኙ ባልና ሚስት እንደማንኛውም ሰው ‹ልጅ› ብቻ ሊሠጣቸው አልፈለገም፡፡ ‹‹ከሴቶች ከተወለዱት ሁሉ ከእርሱ የሚበልጥ ማንም አልተነሣም›› ተብሎ በጌታ የተነገረለትን ፤ ነቢይ ፣ ሐዋርያ ፣ ባሕታዊ ፣ ሰባኪ ፣ ካህን ፣ ሰማዕት ሊሠጣቸው ፈለገ፡፡ በኦሪት መቅደስ የሚያጥን ሳይሆን በባሕር መካከል አምላኩን የሚያጠምቅ ቅዱስ ልጅ ሊሰጣቸው ፈለገ፡፡ ከእናቱ ማኅጸን ስብከት የሚጀምር ከሞተም በኋላ ስብከቱ ከዳር ዳር የሚሰማ መምህር ፣ የሙሽራው ክርስቶስ ሚዜ ፣ ከፀሐይ በፊት ያበራ ጨረቃ ፣ ከቃል መምጣት በፊት የተሰማ ድምፅ ፣ በመወለዱ የብዙዎች ደስታ ምክንያት የሆነ ዮሐንስን ሊሠጣቸው ፈለገ፡፡ ዘካርያስና ኤልሳቤጥ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስን ለመውለድ ጌታ ሊወለድ ስድስት ወር እስኪቀረው ድረስ መጠበቅ ነበረባቸው፡፡ ‹ነገርን ሁሉ በጊዜው ውብ አድርጎ የሠራ› እግዚአብሔር በኀዘን ድባብ የኖረውን የእነዚህን ጻድቃን ቤት ዳግም በጊዜው ውብ አድርጎ ሠራው፡፡ እንዲህ ዓይነቱን ልጅ ለመውለድ ከሆነስ እንኳንስ ማርጀት መሞትም አያስቆጭም፡፡

አንድ ነገር እንጨምር፡፡ ቅዱስ ገብርኤል ለዘካርያስ ‹ጸሎትህ ተሰምቶልሃል› ሲለው ዘካርያስ የደነገጠው ከጊዜው ርዝመት የተነሣ ተስፋ ቆርጦ ጸሎቱን ዘንግቶት ስለነበር ነው፡፡ ዘካርያስ የጸለየውን ጸሎት ቢረሳውም እግዚአብሔር ግን አልረሳውም፡፡ ዘካርያስ ማለት የስሙ ትርጉም ‹እግዚአብሔር ያስታውሳል› ማለት ነው፡፡
የጻድቃን ወላጆቹ እና የመጥምቁ በረከት ከሁላችን ጋር ይሁንልን፡፡ ቅዱስ ያሬድ ‹ዮሐንስ እዴከ መጥወኒ› ‹ዮሐንስ እጅህን ሥጠኝ› እንዳለ መድኃኔዓለምን ባጠመቁ ቅዱሳት እጆቹ ሁላችንን ይባርከን ዘንድ ጸሎታችን ነው።

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ሰኔ 30 2007 ዓ.ም.
177 views03:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-09 06:36:52 ++ ‹‹እግዚአብሔር ያስታውሳል›› ++

በሉቃስ ወንጌል መጀመሪያ ላይ ታሪኩ ተመዝግቦ የሚገኘው የመጀመሪያው ቤተሰብ የካህኑ ዘካርያስ ቤተሰብ ነው፡፡ በወንጌል መጀመሪያ ላይ የምናገኘው ይህ ካህን (በኦሪት መጀመሪያ ላይ እንደሚገኘው ካህን እንደ አሮን ሁሉ) የሚስቱ ስምዋ ኤልሳቤጥ ነው፡፡ (ዘጸ. 6፡23) ዘካርያስና ኤልሳቤጥ ‹በሰው ፊት ያለ ነውርና ያለ ነቀፋ› የሚሔዱ ሲሆን ልብንና ኩላሊትን በሚመረምረው ‹በእግዚአብሔር ፊት ደግሞ ጻድቃን ነበሩ› ይላል ወንጌሉ፡፡

ካህኑ ዘካርያስ እና ሚስቱ ኤልሳቤጥ እንደማንኛውም ባልና ሚስት ልጅ ለመውለድ የተመኙት በወጣትነታቸው ጊዜ ነበር፡፡ በተለይም ክህነት በዘር ሐረግ ብቻ በሚተላለፍበት በዚያ ዘመን ከአሮን የልጅ ልጅ ከአብያ ቤተሰብ የሆነው ዘካርያስ ወንድ ልጅ ወልዶ ልጁ እሱ በሚያገለግልበት መቅደስ ተተክቶ እንዲያገለግል ይመኝ ነበር፡፡ ይሁንና ሚስቱ ኤልሳቤጥ መካን ነበረች፡፡

መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚያስረዳን መካንነት በወንድም በሴትም ሊከሰት ይችላል፡፡ ‹‹የተባረክህ ትሆናለህ ፤ በሰዎችህም ሆነ በእንስሳትህ ዘንድ ሴት ብትሆን ወይም ወንድ መካን አይሆንብህም›› የሚለው ቃል መካንነት በወንድም ሊከሰት እንደሚችል ያስረዳናል፡፡ (ዘዳ. 7፡14) በመጽሐፍ ቅዱስ ሰባት መካን ሴቶች ተጠቅሰዋል፡፡ እነዚህም ሣራ ፣ ርብቃ ፣ ራሔል ፣ አንትኮዬ (የሶምሶን እናት) ፣ ሃና (የሳሙኤል እናት) ፣ ሜልኮል እና ኤልሳቤጥ ናቸው፡፡ ከእነዚህ ሰባት መካን ሴቶች ውስጥ ያልወለደችው የዳዊት ሚስት የሳኦል ልጅ ሜልኮል ብቻ ስትሆን ያልወለደችበት ምክንያት መካንነትዋ የመጣው በእግዚአብሔር ታቦት ፊት የሚዘምረው ባልዋን ዳዊትን ስለናቀችውና አሽሙር ስለተናገረች ነበር፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ልጅ ባለመውለድ የተጠቀሰችው ሌላ ሴት ሱነማዊቷ ሴት ስትሆን ያለመውለድዋ ምክንያት በባልዋ ሽምግልና ምክንያት እንጂ በእርስዋ አለመሆኑ አብሮ ተጽፎአል፡፡ (2ነገሥ. 4፡14)

ኤልሳቤጥ ልጅ ካለመውለድዋ ይልቅ ትልቅ ስቃይ የሆነባት የሰዎች ነቀፌታ ነበር፡፡ በዚህ መሰቃየቷን የምንረዳው ከጸነሰች በኋላ እንኳን ጸነስኩ ብላ ለመናገር ተሳቅቃ አምስት ወራት ያህል ጽንሱን መሰወርዋ ነው፡፡ በእርግጥም ብዙዎች ከመካንነት በላይ ስቃይ የሚሆንባቸው የሰዎች ክፉ ንግግር ነው፡፡‹መቼ ነው የምትወልዱት?› ‹ትዳር ያለ ልጅ እንዴት ይሆናል?› ‹እስካሁን አልወለድሽም?› እየተባሉ በጥያቄ የሚቆስሉ ብዙዎች ናቸው፡፡ አልፎ ተርፎም በአሽሙር የሚሰደቡ ፣ በነገር ጅራፍ የሚገረፉ ብዙዎች ናቸው፡፡ ለዚህ ጥሩ ምሳሌ የምትሆነን ጣውንትዋ ፍናና ታስቆጣትና ታበሳጫት የነበረችው ሃና ናት፡፡ ሃና ባለመውለድዋ በሚደርስባት ነቀፋ ምክንያት እህል እንኳን አስጠልቷት አትቀምስም ነበር፡፡ ደግነቱ ባልዋ ሕልቃና አለመውለድዋን አይቶ አልናቃትም ይልቁንም ‹‹ለምን ታዝኚአለሽ? ለምንስ እህል አትቀምሺም? ከአሥር ልጆች እኔ አልሻልሽም?›› ብሎ የሚያጽናና መልካም ባል ነበረ፡፡ (1ሳሙ. 1፡4-8)

ኤልሳቤጥም የገጠማት ይህ ዓይነቱ ፈተና ነው፡፡ መካን መሆንዋ ብቻ ሳይሆን የሊቀ ካህናቱ ዘካርያስ ሚስት ሆና አለመውለድዋ የበለጠ ፈተና ነበር፡፡ ሰው መቼም በሰው ለመፍረድ ብዙ አይቸገርም፡፡ ‹ባልዋ በቤተ መቅደስ እያገለገለ እግዚአብሔር ልጅ የነሣቸው ክፉዎች ቢሆኑ ነው እንጂ›› ብሎ ማሰቡም አይቀርም፡፡ ዘካርያስ ካህኑ ግን በሚስቱ በኤልሳቤጥ ላይ አንዳች ክፉ ቃል አልተናገረም ፤ ተናግሮ ቢሆን ኖሮም ‹ሁለቱም ጻድቃን ነበሩ› ባልተባለለት ነበር፡፡ የሚገርመው ዘካርያስ በመልአኩ በቅዱስ ገብርኤል ፊት እንኳን ‹እኔ ሽማግሌ ነኝ ፤ ሚስቴም አርጅታለች› አለ እንጂ ስለ ‹ሚስቴ መካን ናት› ብሎ አንዲትም ቃል አልተናገረም፡፡

እነዚህ ጻድቃን ባልና ሚስት ልጅ ተመኝተው ባያገኙም ‹ሁለቱም በእግዚአብሔር ፊት ጻድቃን ነበሩ› ይላል፡፡ ልብ አድርጉ ልጅ ሳይኖራቸው ፣ በኑሮአቸው ደስተኛ ሳይሆኑ በፈጣሪ ሕግና ትእዛዝ መሔድ መቻላቸው በጣም ከባድ ነው፡፡ በሰው ፊት ፈጣሪን ላለማማረር የሆዳቸውን በሆዳቸው ይዘው በውስጣቸው ሊሳደቡ አልሞከሩም፡፡ ‹‹ምነው ፤ ምን አደረግንህ?›› እንኳን ብለው ፈጣሪያቸውን አልወቀሱም፡፡ በስቃይ ውስጥ ሆነው እንኳን ልብን በሚመረምረው አምላክ ፊት ‹ጻድቃን ነበሩ›፡፡ ቤት በልጆች ሳቅ ተሞልቶ ፣ ጤንነት ተሟልቶ ፣ ሀብት ንብረት ሳይጎድል እግዚአብሔርን ማምለክ ብዙ ላያስቸግር ይችላል ፤ በማጣት ፣ በመከራ ፣ በመሰደብ ውስጥ እየኖሩ ጻድቅ ሆኖ መገኘት ግን እጅግ አስደናቂ ነው፡፡

ዘካርያስና ኤልሳቤጥ ልጅ ለመውለድ ፈጣሪን ሲማጸኑ ቢኖሩም የወጣትነታቸው ዘመን ግን አለፈ፡፡ ኤልሳቤጥ የሆድዋን ፍሬ ሳትመለከት ፣ ዘካርያስ የአብራኩን ክፋይ ሳያይ ፣ እንደ ካህናት ልማድ ልጁን ለቤተ መቅደስ አገልግሎት ሳይተካ ሁለቱም አረጁ፡፡ ‹‹እባክህ ፈጣሪ ሆይ ልጅ ሥጠን›› ብለው እየለመኑ ዓመታት አለፉ፡፡ ከብዙ ዓመታት በኋላ ግን ቅዱስ ገብርኤል መጥቶ ‹ዘካርያስ ሆይ ጸሎትህ ተሰምቶልሃልና አትፍራ ሚስትህ ኤልሳቤጥ ልጅን ትወልድልሃለች› አለው፡፡ ዘካርያስ ግራ ገባው ፤ ከጸለየው ዓመታት ያለፈው ጸሎቱን ፣ ከተመኘው ዘመናት ያለፈው ምኞቱን አሁን ‹ተሰምቶልሃል› ሲባል ለደስታ አቅም አጠረው፡፡

ነቢዩ ዳንኤል ፈጣሪውን ሲለምን ወዲያው መልስ አልመጣለትም ነበር ፤ ከሃያ አንድ ቀን በኋላ ግን ቅዱስ ገብርኤል መጥቶ ‹ሰይጣን ከመንገድ አዘግይቶኝ ነው እንጂ ወደ አንተ የተላክሁት በዕለቱ ነበር› አለው፡፡ ዳንኤልም ሃያ አንድ ቀን ቢዘገይም እንኳን ገና ጸሎቱን አላቋረጠም ነበርና ከሦስት ሳምንት በኋላ የጸሎቱን መልስ ማግኘቱ ብዙም ግራ አላጋባውም፡፡ (ዳን.10፡12) ቅዱስ ገብርኤል ወደ ዘካርያስ መጥቶ ‹ጸሎትህ ተሰማ› ያለው ግን እንደ ዳንኤል ከሃያ አንድ ቀን በኋላ አይደለም፡፡ ከሃያ አንድ ዓመታት በኋላም እንኳን አይደለም፡፡ ዘካርያስ ሽማግሌ እስኪሆን ፣ ኤልሳቤጥም እስክታረጅ ድረስ ቆይቶ የወጣትነት ዘመኑን ጸሎት ነው ‹ተሰምቶልሃል› ያለው፡፡ ስለዚህ ዘካርያስ ‹ስእለቴ ሰመረ› ለማለት እንኳን ግራ ተጋባ፡፡

እግዚአብሔር አሠራሩ እንዲህ ነው ‹‹እርሱም አይዋሽም ቢዘገይም በእርግጥ ይመጣልና ታገሠው እርሱ አይዘገይም።›› ተብሎ እንደተጻፈ እግዚአብሔር መልስ የሚሠጥበት ጊዜ በሰው ሕሊና የሚመረመር አይደለም፡፡ (ዕን. 2፡3) የለመንነውን ነገር ሳያደርግልን ልናረጅ ፣ ልንሸመግል እንችላለን፡፡ ከዚያም አልፎ የተመኘነውን ነገር ሳይሠጠን ልንሞትም እንችላለን፡፡ ፈቃዱ ከሆነ ግን የጸሎታችንን መልስ ከመቃብር ቀስቅሶ ሊሠጠን ይቻለዋል፡፡ ይህን የማያምን ሰው ሙሴን መጠየቅ ይችላል፡፡

ሙሴ እግዚአብሔርን ‹ክብርህን አሳየኝ› ብሎ ለመነ ፤ እግዚአብሔርም ‹‹በዓለት ላይ አቆምሃለሁ ... ጀርባዬን ታያለህ ፊቴን አታይም›› ብሎ መለሰለት፡፡ ሙሴ ይህን እግዚአብሔርን ሳያይ ወደ መቃብር ወረደ፡፡ ሊሞት ሲል እንኳን ‹ያልከኝን ሳታሳየኝ› ብሎ ሳይጠይቅ የዋሁ ሙሴ ወደ መቃብር ገባ፡፡ በመቃብር ውስጥ ሆኖ በሺህ የሚቆጠሩ ዓመታት አሳለፈ፡፡ ከዘመናት በኋላ ግን ሙሴ በታቦር ተራራ ዓለት ላይ እንዲቆም ተጠራ፡፡ ‹ክብርህን አሳየኝ› ብሎ ለለመነው ልመና መልስ ተሠጠው፡፡ በታቦር ተራራ ‹አንድ ልጅም በአባቱ ዘንድ እንዳለው ክብር ያለውን ክብሩን አየ› የብሉይ ኪዳን ሰው ሆኖ ሳለ የሐዲስ ኪዳን ዕድል
138 views03:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-07 09:22:22
መበለተ ቅዱስ ሊቅነ ቤተ ያሬድ ኢትረውይኑ ንስቲተ?

እስመ እንታክቲ ትዌስክ እምድሩ መልዕልተ እሳት እሳተ።
350 viewsedited  06:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ