ግብፅ በኤርትራ የባህር ግዛት ላይ ፈቃድ ሳይኖራቸው በመገኘታቸው የተያዙት ግብፃውያን ዓሳ አጥማጆች እንደሆኑ በመጥቀስ ዜጎቿ እንዲለቀቁ የኤርትራን መንግሥት ጠየቀች።
በአምስት ጀልባዎች በመሆን በኤርትራ የባህር ክልል ውስጥ ሲንቀሳቀሱ የተገኙትን ግብፃዊያን የኤርትራ የባህር ኃይል በቁጥጥር ሥር ያዋለው ባለፈው ወር መሆኑን መረጃዎች የሚያመለክቱ ሲሆን፣ ‹‹ዓሳ አጥማጆች ናቸው›› የተባሉትን ግብፃዊያን ለማስለቀቅም የግብፅ መንግሥት ኦፊሳላዊ ጥያቄ ለኤርትራ መንግሥት ማቅረቡ ተሰምቷል።
[Reporter]
@YeneTube @FikerAssefa