ምዕራፍ 2 በክርስቶስ ያለ ምክርን እንፈጽም ወደ ፊሊጲስዮስ 2: 1-4 1 በክርስቶስም አንዳች | Yeka Abado Full Gospel Belivers'church
ምዕራፍ 2
በክርስቶስ ያለ ምክርን እንፈጽም
ወደ ፊሊጲስዮስ 2: 1-4
1 በክርስቶስም አንዳች ምክር ቢሆን፥ የፍቅር መጽናናት ቢሆን፥ የመንፈስ ኅብረት ቢሆን፥ ምሕረትና ርኅራኄ ቢሆኑ፥ ደስታዬን ፈጽሙልኝ፤
2 በአንድ አሳብ ተስማሙ፥ አንድ ፍቅር አንድም ልብ አንድም አሳብ ይሁንላችሁ፤
3 ለወገኔ ይጠቅማል በማለት ወይም በከንቱ ውዳሴ ምክንያት አንድ እንኳ አታድርጉ፥ ነገር ግን እያንዳንዱ ባልንጀራው ከራሱ ይልቅ እንዲሻል በትሕትና ይቍጠር፤
4 እያንዳንዱ ለራሱ የሚጠቅመውን አይመልከት፥ ለባልንጀራው ደግሞ እንጂ።
I. በክርስቶስም አንዳች ምክር ቢሆን፥ ምን አይነት ምክር ነው? ጳውሎስ ደስታዬን ፈጽሙልኝ ያሰኘው-
1. የፍቅር መጽናናት
2. የመንፈስ ኅብረት
3. ምሕረትና ርኅራኄ
እነዚህ ፍቅር፤ ኅብረት፤ ምህረትና ርህራሄ በክርስቶስ ውስጥ ያየናቸው ባህሪያት ናቸው ስለዚህ እነዚህ ባህርያት በመንፈስ ቅዱስ በኩል ዛሬ በእኛ ይገለጣሉ:: በፍቅር ተመላለሰ ደግሞም ከዚህ የሚበልጥ ፍቅር ለማንም የለውም የተባለለትን ትልቅ መስዋዕትነት ከፈል:: ከአባቱም ጋር ህብረት ነበረው ለሊቱን ሁሉ ሲጸልይ ያድራል:: ምህረትና ርኅራሄውም በደንብ ታይቷል:- ከሳሾችሽ ወዴት አሉ? እኔም አልፈርድብሽም ሂጂ ሲል በሌላ ቦታ ደግሞ እረኛ እንደሌላቸው ተበትነው ሲያይ አዝኖ:: ለታመሙት ራርቶ የሚፈውስ ከሚያለቅሱት ጋር የሚያለቅስ ሩህሩህ ጌታ:: ብዙ ማለት ይቻላል ስለ እየሱስ ይህ በርሱ የተጀመረው ህይወት አሁንም በእኛ ይቀጥል::
II. በአንድ አሳብ ተስማሙ፥ ምን ብናደርግ ነው በአንድ ሀሳብ ልንስማማ የምችለው?
1. አንድ ፍቅር – ክርስቶስን ብቻ ማየት እንዴት እንደወደደን
2. አንድም ልብ – ክርስቶስ እንዲከብር ብቻ ማሰብ
3. አንድም አሳብ – እርሱን በሀሳባችን ሁሉ መቀደስ ያኔ እርሱን ብቻ ለማክበር እንስማማለን
4. በትሕትና – ሰውን ሁሉ በክርስቶስ ውስጥ ማወቅና ከኔ ይሻላል ማለት
5. ለሌላው በማሰብ – በሌላው ውስጥም ጌታ ይሰራል ብሎ መቀበልና መርዳት ወደ ተጠሩበት ነገር እንዲደርሱ
በዚህ ሁሉ ውስጥ ዝቅ ማለትና በትህትና መመላለስ አለብን እኔ አውቃለሁን ትተን ከኔ ይሻላል ወገኔ እንበል:: ያለ ሌላው አገልግሎት እኔ የምሮጠው ሙሉ እንድማይሆን ማወቅ:: እግዚአብሔር ለትሁታን ጸጋን ይሰጣልና::