Get Mystery Box with random crypto!

የእዉነት ግጥም። ሙሉቀን የጀሚላ✍✍✍

የቴሌግራም ቻናል አርማ truzmulukenyegmila — የእዉነት ግጥም። ሙሉቀን የጀሚላ✍✍✍
የቴሌግራም ቻናል አርማ truzmulukenyegmila — የእዉነት ግጥም። ሙሉቀን የጀሚላ✍✍✍
የሰርጥ አድራሻ: @truzmulukenyegmila
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 378
የሰርጥ መግለጫ

በዚች ሄደት መለስ በበዛበት ዓለም
ዉሸትን ቀበሮ እዉነትን ተናግሮ የሞተ የለም
አምላክ ላስተሳስብ በሰጠን አምሮ
የተጎዳ የለም ዉሸትን ሸሽጎ እዉነትን ተናግሮ።
@እዉነትን ለማወቅ ትልቅ ጥረት ይጠይቃል
@እዉነትን ለመናገር ደሞ ትልቅ ድፍረት ይጠይቃል
@እዉነትን ለመኖር ደሞ ትልቅ መስዋዕት ያስከፍላል።
@Truzmulukenyegmila
ግጥም ለመላክ
@Mulukenyejmila
✍ሙሉቀን የጀሚላ

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-05-18 07:29:20 ሰላም ዉድ የቻናሌ ቤተሰቦች ያዉ ሰዉ ሁኖ የዉልደቱን ጊዜ ማያስብ የለም በርግጥ የእድሚያችን ጭማሪ ስናስብ ሞታችን መቃረቡ ነዉ ቢሆንም ግን ካለን ጊዜ ላይ ፈጣሪ እንድናስብ እናም ደሞ እንድናመሰግነዉ ጊዚያችንን መጨመሩ ተመስጌን ያስብላል ይሄዉ እኔም እድሜክ ስንት ነዉ ብላቹሁ አትጠይቁኝና ዛሬ የተወለድኩበት ቀን ነዉ።
እናም ተመስጌን ለዛሬዋ ቀን ስለበቃዉ።

H.B.D to me
162 viewsሙሉቀን የጀሚላ 777 @Truzmulukenyegmila, 04:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-12 13:10:56
አፈር ገፊ

በሬዎችን ጠምዶ አፈሩን ገፍቶ
ፍሬ እንዲያፈራ እህልን ዘርቶ
..........
.........
.......

ሙሉቀን የጀሚላ

@Mulukenyejmila

@Truzmulukenyegmila
264 viewsሙሉቀን የጀሚላ 777 @Truzmulukenyegmila, 10:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-02 09:59:28 ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለኢድ ዓል-ፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ
.
.
.
@Truzmulukenyegmila
311 viewsሙሉቀን የጀሚላ 777 @Truzmulukenyegmila, 06:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-29 21:27:51 "እንደ #ንስር

የሆነ ቀን በናሽናል ጂኦግራፊ ንስር መርዛማውን ኮብራ እባብ ሲያድን ተመልክቼ ግራ ተጋባሁ፡፡ እባቡ ግዙፍ እና አደገኛ ሆኖ ሳለ እንዴት በንስሩ ሊሸነፍ ቻለ? አልኩኝ፡፡
መልሱ ግልጽ ነው፡፡ ንስሩ መጫወቻ ሜዳውን ያውቃል!! ምናልባት ንስሩ እና እባቡ መሬት ላይ ቢገናኙ ኖሮ እባቡ አሸናፊ ንስሩ ደግሞ ተሸናፊ ይሆኑ ነበር፡፡ ንስሩ እባቡን ከላይ ወደታች ተመለከተ፡፡ እባቡን ሲገጥመውም ከመሬት ወደላይ ወሰደው፡፡ የንስሩ መርህ መጫወቻ ሜዳን መለየት ነው!!

እባብ መሬት መጫወቻ ሜዳው(አለሙ) ነው፡፡ መሬት ላይ እባብ ሃይለኛና አሸናፊ ነው፡፡ የንስሩ መጫወቻ ሜዳ (አለም) ደግሞ ከፍታ ነው፡፡ የከፍታን አለም ከማንም በላይ ያውቀዋል፡፡ በሜዳው ድል ማድረግንም ይችልበታል!!

ንስር ይህን ጠንቅቆ ያውቃልና እባቡን ከራሱ አለም አንፃር ተመለከተው፡፡ ቀጥሎም ተጋጣሚውን ከአለሙ (መሬት) ነጥሎ ወደራሱ አለም ወሰደው፡፡ በገዛ ሜዳውም ድልን ተቀናጀ!!

ወዳጄ ሆይ በየትኛውም መስክ ድልን ከፈለክ እንደ ንስር ሁን!! መጫወቻ ሜዳህን ለይ፡፡ አለምህን በትክክል እውቅ፡፡ ካንተ አለም አንፃር መመልከትን ተለማመድ!! ከምንም በላይ በምንም ምክንያት በተጋጣሚክ መጫወቻ ሜዳ ላይ አትፋለም፡፡ ያለህን አቅም ሁሉ ተጠቅመህ ተጋጣሚህን ወደ ራስህ መጫወቻ ሜዳ ውስደው!!!!!!

@Truzmulukenyegmila
286 viewsሙሉቀን የጀሚላ 777 @Truzmulukenyegmila, 18:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-28 19:34:15 † † †

▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬

መረጃ ዘተዋሕዶ !

በዛሬው ዕለት የወራቤ ቅዱስ ሩፋኤል ቤተ ክርስቲያንን ጽንፈኞች ወደ አካባቢው በመጓዝና ማንም እንዳይቀርብ በማስፈራራት ጉልላቱን በማውረድ ካፈረሱ በኋላ አቃጥለውታል። በከተማዋ የሚገኙ ኦርቶዶክሳውያንም ላይ ድብደባ ሲፈጸምባቸው ውሏል። ተጨማሪ መረጃዎችም በመውጣት ላይ ይገኛሉ።

የጸረ ኦርቶዶክሳዊው አገዛዝ ራስ በተደጋጋሚ ሃይማኖታዊ ግጭት እንዲነሳና በኦርቶዶክሳውያን ላይ እልቂት እንዲፈጸም ሁኔታዎችን ከማመቻቸት ጀምሮ እጅግ የሚጠላት የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን እንድትጠፋ ለማድረግ ጽንፈኛ ጂሃዲስት ሃይሎች ያለ ምንም ከልካይ እንዲደራጁና እንዲንቀሳቀሱ በማድረግ ሃገሪቱን እጅግ አስከፊ ወደሆነ አቅጣጫ እየመራት ይገኛል።

-----------------------------------------------------
ጽንፈኞች የጥፋት አዋጅን በማህበራዊ ሚዲያዎች እያሠራጩ በመሆኑ መላው ኦርቶዶክሳዊ ስለ ቅድስት ቤተክርስቲያን ሁኔታዎችን በንቃት ይከታተል ዘንድ እየተጠየቀ ይገኛል።
-----------------------------------------------------

▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬


@Truzmulukenyegmila
266 viewsሙሉቀን የጀሚላ 777 @Truzmulukenyegmila, 16:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-28 19:06:45 ሰው ምንድነው ቢሉ ደጋግሞ ያሰበውን ነው ይባላል፤ ስለዚህ ለማን ብለህ ነው አብዝተህ የጎደለህን ከሰው ያሳነሰህን የምታስበው?!

በቃ ተዓምር መስራት እንደምትችል ባንተ ምክንያት መጀመሪያ የራስህ ከዛ የቤተሰቦችህ ህይወት እንደሚቀየር አስብ እሱን እውነት ለማድረግ የምትችለው ጥግ ድረስ ጣር የቀረውን ለፈጣሪ ተወው!

ሰናይ ምሽት ተመኘንላችሁ
@Truzmulukenyegmila
310 viewsሙሉቀን የጀሚላ 777 @Truzmulukenyegmila, 16:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-27 09:23:19 የእዉነት ግጥም

#ማነው_የጎዳህ?

አብርሃም ሊንከን ወደ አሜሪካን ፕሬዝዳንትነት በመጣበት ጊዜ አባቱ ጫማ ሠሪ ነበር። በፅንፈኞች ዘንድም *የጫማ ሠሪ ልጅ* ወደ ፕሬዝዳንትነት መምጣቱ ያልታሰበና ብዙዎቹንም ያስከፋ ነበር። በበአለ ሲመቱ ቀንም አብርሃም ሊንከን የመጀመሪያ ንግግሩን ሊያደርግ በምክር ቤት ተገኘ። ድንገትም ከመሐል አንድ ባላባት ተነሣና፦ "አብርሃም ሊንከን ሆይ፥ አባትህ ለቤተሰቤ ጫማ እንደሚሠራ ልትዘነጋ አይገባም" ሲል ምክር ቤቱ በአንድ አፍ ሳቀ፤ ባላባቱ አብርሃም ሊንከን ላይ አላገጠበት ብለው አስበዋልና።

አንዳንድ ሰዎች ግን ሲፈጥራቸውም ልዩ አርበኛነትን ተላብሰዋልና ሊንከን ያላገጠበትን ሰውዬን ዐይን ዐይኑን እያየ እንዲህ አለ፦ "ጌታዬ ሆይ፥ አባቴ ለቤተሰብዎ ጫማ እንደሚሠራ አውቃለሁ፤ በዚህ ምክር ቤት ውስጥ ለሚገኙ ለበርካቶችም ጭምር፤ ምክንያቱም እሱ ጫማ እንደሚሠራው ማንም ሰው አይሠራምና። እሱ ፈጣሪ ነው። የርሱ ጫማዎች ጫማዎች ብቻ አይደሉም፤ ነፍሱን በመላ ያፈሰሰባቸው የተሰጥኦ ውጤት እንጂ። እስቲ ልጠይቆት፣ አባቴ በሚሠራቸው ጫማዎች ቅሬታ አለዎት? - ምክንያቱም እኔ የጫማ ሙያን ጠንቅቄ ስለማውቅ ምንም አይነት ቅሬታ ቢኖርዎት ሌላ ጫማ ልሠራሎት እችላለሁ። ይሁንና እኔ እስከማውቀው ድረስ ማንም ሰው በአባቴ ጫማዎች ላይ ፈፅሞ ቅሬታ አቅርቦ አያውቅም። እጅግ ብልህና ታላቅ ሥራ ፈጣሪ ስለሆነ እኔም በአባቴ እኮራለሁ"። ምክር ቤቱ ረጭ አለ፤ ሁሉም ሰው አንገቱን አቀረቀረ።

ልብ በል፤

• ፍቃድህን ካልሰጠኸው በቀር ማንም ሊጎዳህ አይችልም።

• ምንጊዜም ቢሆን፤ የገጠመን ነገር ሳይሆን ለገጠመን ነገር/ጉዳይ የሰጠነው ምላሽ ነው እኛን የሚጎዳን።

• መርከቦች ዙሪያቸውን በከበባቸው ውሃ አይሰጥሙም፣ ወደ ውስጣቸው በሚያስገቡት ውሃ እንጂ፤ ልክ እንዲሁ በዙሪያህ እየሆነ ያለውን ነገር ወደ ውስጥህ እንዲገባና ተጭኖም እንዲጥልህ አታድርግ።

ማንም ሰው ይሁን ምንም ነገር አንተን ሊጎዳ የሚችለው ፍቃድህን ከሰጠኸው ብቻና ብቻ ነው!!

መልካሙን ተመኘዉላቹሁ

@Mulukenyejmila

@Truzmulukenyegmila
329 viewsሙሉቀን የጀሚላ 777 @Truzmulukenyegmila, 06:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-26 21:52:57 ጣፋጭ ውሸት
የሚጣረሱ ሀሳቦችን የመያዝ ባህሪ
(Cognitive Dissonance)

አንድ ቀበሮ የወይን ፍሬ ያይና ለመብላት ይቋምጣል። ሙክክ ብሎ የበሰለውን ትልቅ ፍሬ ለማውረድም ተንጠራራ፡፡ የፊት እግሩን የወይን ግንዱ ላይ አስደገፈና አንገቱን ወደ ፍሬዋ አንጠራራ፤ ሊደርስባት ግን አልቻለም፡፡ በዚህ እየተናደደ እንደገና እድሉን ለመሞከር ወሰነ ፤ ራሱን በሚገባ አዘጋጅቶ ወደ ላይ ተወረወረ። አፉ ግን ቀዝቃዛ አየር ብቻ ቀዝፎ ተመለሰ፡፡ ለሶስተኛም ጊዜም ዘሎ ቢሞክር ወደ ኋላ ወደቀና ተፈጠፈጠ፡፡ ፍሬው ይቅርና አንዲት ቅጠል እንኳን ግን አልወደቀችም፡፡ ቀበሮውም አፍንጫውን አዞረና ‹‹ይህ ፍሬ ሲጀምር አልበሰለም፤ ለጎምዛዛ ፍሬ እንዲህ የሚያደርገኝ ምንድን ነው? ብሎ ወደ ጫካው ፈረጠጠ፡፡" -

ግሪካዊው ገጣሚ አይሶፕ የተለመዱ የምክንያታዊነት ስህተቶች ከሆኑት መካከል አንዱን ለማስረዳት ይህንን አፈ ታሪክ ፈጥሮ ነበር፡፡ ይህም የአስተሳሰቦች መጣረስ ነው፡፡ እሱ በፈጠረው በዚህ ታሪክ ውስጥ የቀበሮው የአስተሳሰብ መጣረስ የተፈጠረው ቀበሮውን የሆነ ነገር ለማድረግ ሲፈልግና አልሳካለት ሲለው ነው፡፡ ይህ ታሪክ ከሚከተሉት ሶስት መንገዶች መካከል በአንዱ ውስጥ ማለፉ የግድ ነው፡፡ አንደኛው መንገድ እንደ ምንም ብሎ ፍሬዋን ማውረድ ነው። ሁለተኛው ችሎታው በቂ አለመሆኑን አምኖ መቀበል፣ ሶስተኛው ደግሞ የተፈጠረውን ነገር ወደ ኋላ ተመልሶ እንደገና በመተርጎም ሃሳብ መቀየር ነው፡፡ #የመጨረሻው አማራጭ የሚጣረሱ አስተሳሰቦችን ችግር የመያዝ የእሱ ነጸብራቅ ምሳሌ ነው። (Cognitive Dissonance)

በቅርቡ የአሸባሪው የህውሀት ቡድን አመራሮች በነፃ መለቀቃቸው ይታወቃል።ይህ በብዙሀኑ ህዝብ ዘንድ ትልቅ መደናገረን ፈጥሯል።መጀመሪያ መንግስት በህውሀት እና እሱን በሚደገፋ ምዕራብውያን ላይ ከፍተኛ ህዝባዊ ዘመቻ ማድረጉ ይታወሳል። በየሚዲያውም ህውሃት ለመስማትና ለማየት የሚቀፉ ግፎችን በንፁሀን ህዝብ ላይ እንደፈፀመ እያሳዩን ነበር። አሁን ደግሞ ጦርነቱ ባልተጠናቀቀበት እና ህውሀት ይበልጥ ለመዋጋት በተዘጋጀበት ጊዜ ለነዚህ ሰዎች ምህረት እና ይቅርታ ማድረግ እንዳለብን ይነግሩናል። እውነታው ግን መንግስት ርህራሄ ወይም ሰብዓዊነት ተሰምቶት ሳይሆን የምዕራባውያን ጫናን መቋቋም ስላልቻለ ይመስለኛል። የከሰረ የዲፕሎማሲ አቋሙ ብዙ ዋጋ አስከፍሎታል። እናም ይህንንን ችግሩን ሽፋን ለመስጠት ስለ ይቅርባይነት እና ስለ ምህረት ከክርስቶስ በላይ ሊሰብከን ይሞክራል።መንግስት ስህተቱን ማመን አይፈልግም። ከዚህ በተቃራኒው የወሰነው ውሳኔ ብዙ ችግሮችን እያስተናገደም እንኳን ቢሆን ሰላም የሚያመጣ ውሳኔ እንደሆነ ይነግረናል። በየጊዜውም ይህንን ኢ-ምክንያታዊ አቋሙን የሚደግፍለትን ጣፋጭ ውሸት ይፈበርካል።

ገጣሚው እንዲህ ይላል
"የጎበዙን ቀበሮ ጨዋታ የፈለግከውን ያህል መጫወት ትችላለህ፣ በዚህ መንገድ ግን የወይኑን ፍሬ አታገኘውም::"

መነሻ ሀሳብ
(The Art of clearly thinking)
ሮልፍ ዶብሊ

መልካም ምሽት ተመኘዉላቹሁ

@Truzmulukenyegmila
222 viewsሙሉቀን የጀሚላ 777 @Truzmulukenyegmila, 18:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-26 21:50:44 ግሩም ጥቅሶች

1.‹‹ አዋቂ ሠው ሁለት ልብ አለው፡፡ አንዱ ሲደማበት በሁለተኛው ይታገሳል፡፡››
ካህሊል ጂብራን

2."ችሎታህ የማይዋጥላቸዉ ጠላቶችህ በዉሃ ላይ ስትራመድ ቢያዩህ ዋና ስላማይችል ነዉ ይሉሃል።"
ኦሾ

3."ሁሉም ሰው ሞትን ይቀምሳል ህይወትን የሚቀምሰው ግን በጣም ጥቂቱ ነው።"
ሩሚ

4."በዙሪያህ ያለው ሁሉ ጨለማ ከመሰለህ ወደ ቀልብህ ተመለስና እንደገና ተመልከት፤ምናልባት ብርሃን መሆን ያለብህ አንተ ልትሆን ትችላለህ"!!!
ሩሚ

5."አንድን ነገር መቼም ላላውቀው አልችልም በሚል ስሜት ተማረው፤ስታውቅ ደግሞ መቼም ላጣው እችላለሁ በሚል ስሜት አጥብቀህ ያዘው!!"
ኮንፊሽየስ

6.‹‹ እውነት እርቃኑን በባዶው መራመድ ይችላል፡፡ ውሸት ግን ሁልጊዜ አምሮና ደምቆ መልበስን ይፈልጋል፡፡ ››
ካህሊል ጂብራን

7."ህይወት የግማሽ እስትንፍስ ያህል አጭር ነች፣ ከፍቅር በቀር ሌላ ነገር አትተከል።"
ሩሚ

8.‹‹ ሐዘንና ደስታ የማይነጣጠሉ ነገሮች ናቸው። ሁለቱም አብረው ይመጣሉ፡፡ ነገር ግን አንዱ ብቻውን ከጎንህ ሲሆን አንደኛው መኝታ ቤትህ እንደተጋደመ አትርሳ፡፡»

ካህሊል ጂብራን

9."ደስታ ዱሪዬ አይደለም። ሰዎች ግን እየመሰላቸው በየመጠጥ ቤቱና በጫት ቤቱ ይፈልጉታል።"
ያልታወቀ

10."እውነተኛ ፍቅር እንደ መናፍስት ነው - ሁሉም ሰው ስለእሱ ይናገራል ፣ ግን ያዩት ጥቂቶች ናቸው።"
ሮቼኩዋል


11." ንግግር ከማድረግህ በፊት ንግግርህን በነዚህ ሶስት በሮች ፈትሸህ አሳልፈው...
ትክክል ነው ወይ?
አስፈላጊ ነው ወይ?
በጎ ነገር ነው ወይ? "
ሩሚ


12." ፍቅር ያልነካው እሱ በጨለማ ውስጥ እንደሚጓዝ ፍጡር ነው "
ፕሉቶ

13."በአለም ላይ ከብዙ ሰው ጋር ትገናኛላችሁ ግን በጭራሽ ከራሳችሁ ጋር ተገናኝታችሁ አታውቁም።"
ኦሾ

14.‹‹ ፍቅርና ደግነት የድክመትና የተስፋ መቁረጥ ምልክቶች ሳይሆኑ የጥንካሬና የውሳኔ ሠጪነት መገለጫ ናቸው፡፡ ››
ካህሊል ጂብራን

15. ‹‹ ፍቅር አልባ ሕይወት አበባ ወይም ፍሬ እንደሌለው ዛፍ ነው፡፡››
ካህሊል ጂብራን



@Truzmulukenyegmila
294 viewsሙሉቀን የጀሚላ 777 @Truzmulukenyegmila, 18:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-26 16:15:43 #ሊሆንም_ላይሆንም_ይችላል!

በአንድ መንደር ውስጥ የሚኖሩ ጠቢብ ሽማግሌ ነበሩ ፡፡ በመንደሩ ውስጥ የነበሩት ነዋሪዎች ጥያቄዎቻቸውን ይዘው እርሳቸው ጋር ይሄዱ ነበር ፡፡

አንድ ቀን በመንደሩ የሚኖር ገበሬ ወደ ጠቢቡ ሽማግሌ መጥቶ ግራ በተጋባ ድምፀት ”እባክዎ ይርዱኝ ፡፡ በጣም አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ነኝ፡፡ በሬዬ ሞተ ስለዚህም የማርስበት እንሰሳ የለኝም ፡፡ ከዚህ የከፋ ምን ሊሆን ይችላል?" አላቸው ፡፡ ጠቢቡ ሽማግሌ በእርጋታ “ከዚህ የከፋ ነገር ሊሆርም ላይኖርም ይችላል።” ብለው ሲመለሱለት ገበሬውም በጥድፊያ ወደ ሰፈሩ ተመልሶ ለጎረቤቶቹ "ሽማግሌው አብዷል፡፡ ከዚህ የባሰ ነገር ምን ሊኖር ይችላል? እንዴት ይህንን ማወቅ ይሳናቸዋል?" አላቸው ፡፡

በነጋታው ገበሬው እርሻ ውስጥ አንድ ፈረስ ይመለከታል፡፡ ምንም በሬ ስላልነበረው “በፈረሱ ባርስስ?” የሚል ሀሳብ ይመጣለታል፡፡ ከዚያ ፈረሱን ይዞ ማረስ ይጀምራል፡፡ ማረስ እንደዛ ቀሎት አያውቅም፡፡ ጠቢቡ ሽማግሌን ይቅርታ ለመጠየቅ ሄደ፡፡ "ልክ ብለው ነበር ፡፡ በሬን ማጣት የመጨረሻው አስከፊ ነገር አይደለም፡፡ እንደውም በረከት ነው፡፡ በሬዬ ባይጠፋ ኖሮ ፈረስ አላገኝም ነበር፡፡ እንደውም በሬዬ መሞቱ በጣም ጥሩ ነገር ነው አይደል?" ሲላቸው። ሽማግሌው በተረጋጋ ድምፀት አሁንም “ምናልባት ሊሆን ይችላል፤ ምናልባት ላይሆንም ይችላል፡፡" ብለው መለሱለት፡፡ ገበሬው እኝህ ሰው አእምሯቸውን ስተዋል ብሎ አሰበ ፡፡

ነገር ግን ገበሬው ቀጣይ የሚፈጠረውን አላወቀም ነበር፡፡ ከጥቂት ቀናት በኋላ የገበሬው ልጅ ፈረሱን እየጋለበ ይወድቅና እግሩ ይሰበራል ፡፡ “እርሻ ላይ ማን ያግዘኛል?” ብሎ ይጨነቅና ሽማግሌው ጋር ይሄዳል ፡፡ “ፈረስ ማግኘቴ ምርጥ ነገር እንዳልነበረ እንዴት አወቁ? ልጄ እግሩ ተሰብሯል፡፡ እርሻ ላይም አያግዘኝም፡፡ ይሄ በርግጠኝነት እጅግ አስከፊ ነገር ነው፡፡ በዚህ መቼም ይስማማሉ፡፡" ይላቸዋል ፡፡ ሽማግሌው ግን ከዚህ በፊት እንዳደረጉት በእርጋታ “ሊሆንም ላይሆንም ይችላል” ብለው ይመልሳሉ፡፡ "አሁንስ መሳሳታቸው እርግጥ ነው!" ብሎ በንዴት ጥሏቸው ይሄዳል፡፡ በነጋታው በመንደራቸው ጦርነት ታውጆ ወታደሮች አቋማቸው ብቁ የሚመስሉ ወጣቶችን በግዳጅ ሰብስበው ይዘው ይሄዳሉ፡፡ ከመንደራቸው የቀረው የሱ ልጅ ብቻ ነበር፡፡ ሌሎቹ ወደ ሞት ቦታ ሲወሰዱ የእርሱ ልጅ በሕህይወት ቤት ቀረ፡፡

ከዚህ ታሪክ ትልቅ ትምህርት እናገኛለን ፡፡ በእውነታው ዓለም ቀጣይ የሚከሰተውን ነገር ማወቅ አንችልም ፡፡ የምናውቅ ይመስለናል እንጂ አናውቅም ፡፡ ቀጣይ ይፈጠራሉ ብለን የምንሰጋቸውን ነገሮች በአእምሯችን ውስጥ እናሰላስላቸዋለን፣ እንጨናነቅባቸዋለን፡፡ ብዙ ጊዜ እንሳሳታለን፡፡ ተረጋግተን ነገሮችን ለመቀበል ከተዘጋጀን ግን ሁሉ ለመልካም ይሆናል ፡፡ አስታውስ አሁን አስቸጋሪ የሚመስልህ ሁኔታ ጥሩ ሊሆንም ላይሆንም ይችላል።

መልካም ዉሎ ተመኘዉላቹሁ

@Truzmulukenyegmila
194 viewsሙሉቀን የጀሚላ 777 @Truzmulukenyegmila, 13:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ