በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊና ቁሳዊ ሀብቶች ላይ ያተኰረ ኢንሳይክሎፔዲያ ሊዘጋጅ ነው
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊና ቁሳዊ ሀብቶች እንዲሁም አስተምህሮዎች ላይ ያተኰረ መዝገበ አእምሮ (ኢንሳይክሎፔዲያ) በማኅበረ ቅዱሳን አማካይነት ሊዘጋጅ መሆኑ ተገልጿል።
የመዝገበ አእምሮ (ኢንሳይክሎፒዲያ) ደረጃውን በጠበቀ መንገድ ለማዘጋጀት እንዲቻል በተለያዩ የሙያ መስኮች የተሰማሩ ምሁራን ዕውቀታቸውንና ልምዳቸውን ማካፈል የሚችሉበት መድረክ በዛሬው እለት በኢሊሌ ኢንተርናሽናል ሆቴል እየተካሄደ ይገኛል።
የሚዘጋጀው መዝገበ አእምሮ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ ፣ ጥንታዊና ሐዋርያዊ አስተምህሮ ፣ ዶግማ ፣ ቀኖና እና ትውፊት እንዲሁም የጳጳሳትን፣ የሊቃውንትን፣ የትልልቅ ገዳማትንና አድባራትን ታሪክ ወዘተ የሚያካትት ይሆናል ተብሎ እንደሚጠበቅ የማኅበረ ቅዱሳን ብሮድካስት አገልግሎት በዘገባው አመልክቷል።
@TikvahethMagazine