በአዲስ አበባ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የሁለት ሰዎች ህይወት አለፈ። በአዲስ አበባ ከተማ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የሁለት ሰዎች ህይወት ያለፈ ሲሆን አደጋው ትናንት ከሌሊቱ 10:00 ሰዓት 24 እየተባለ በሚጠራው አካባቢ ነው የደረሰው፡፡ በደረሰው አደጋ የሁለት ሰዎች ህይወት ወዲያውኑ ሲያልፍ፥ በሁለት ሰወች ላይ ደግሞ ከባድ የአካል ጉዳት ደርሷል፡፡ የአደጋው መንስኤ እየተጣራ መሆኑንም ከአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ኤጀንሲ የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡ @tikvahethmagazine @tikvahmagbot 25.6K viewsedited 08:44