Get Mystery Box with random crypto!

ትምህርት ሚኒስቴር

የቴሌግራም ቻናል አርማ temret_minster — ትምህርት ሚኒስቴር
የቴሌግራም ቻናል አርማ temret_minster — ትምህርት ሚኒስቴር
የሰርጥ አድራሻ: @temret_minster
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 6.79K

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 7

2022-10-09 21:38:19 በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና ለሚወስዱ ተማሪዎች ገለጻ ተሰጠ

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ በተዘጋጁ ሰባት የፈተና መስጫ መዕከላት የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተና ለሚወስዱ ተማሪዎች መስከረም 29/2015 ዓ/ም ገለፃ ተሰጥቷል፡፡

በዕለቱ ተፈታኞች መከተል ስላለባቸው የፈተና ሥነ-ምግባርና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ገለፃ የተሰጣቸው ሲሆን የፈተና ሕግና ደንቦችን አለማክበር በትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ በወጣው መመሪያ መሠረት እርምጃ እንደሚወሰድ ተገልጿል፡፡

በተመሳሳይም በዛሬው ዕለት ለፈታኝ መምህራን አጠቃላይ ገለፃ በዩኒቨርሲቲው ሁሉም ማዕከላት ተሰጥቷል።

በበይነመረብ በተካሄደ መርሃ ግብር ላይም ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ አሕመድና የትምህርት ሚኒስትር ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ፈተናው በስኬት እንዲጠናቀቅ ፈታኝ መምህራን የተጣለባቸውን ሀገራዊ ተልዕኮ በፍጹም ኃላፊነት እንዲወጡ በአጽንኦት አሳስበዋል፡፡

የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት


https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid021zuhguLn2Pw1Fv5ZbcLmsY88fNJuXNnVCmo3wS8Sfkb13TL2EpteNXDUmp2nwkjal&id=100064396371463&sfnsn=mo
922 views18:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-09 20:42:40
የጅማ ዩኒቨርሲቲ ለ12ኛ ክፍል የመጀመሪያ ዙር የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኝ ተማሪዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ  ሰጥቷል።
-------------------------------
የጅማ ዩኒቨርሲቲ በዩኒቨርሲቲው ተመድበው የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ ፈተና ለሚፈተኑ ከ25,000 በላይ  የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኝ  ተማሪዎች ስለፈተናው አሰጣጥ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሰጥቷል።

በዩኒቨርሲቲው ሁሉም ካምፓሶች የግንዛቤ ማስጨበጫ (Orientation) የሰጠ ሲሆን ተፈታኝ ተማሪዎችም በሚሰጣቸው የግንዛቤ ማስጨበጫ መሰረት መመራት እንደሚገባቸው ተብራርቷል፡፡

በግንዛቤ ማስጨበጫው ተማሪዎች ማድረግ ስለባቸውና ስለሌለባቸው ጉዳዮችበፈተና ጣቢያ ኃላፊዎችና አስተባባሪዎች ገለፃ ተደርጎላቸዋል።

የ2014ዓ.ም የ12ኛ ክፍል የመጀመሪያ ዙር የማህበራዊ ሳይንስ ፈተና ነገ መሰጠት የሚጀምር ይሆናል።
880 views17:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-09 17:25:43
የኒቨርስቲዎች በ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና አሰጣጥ ዙሪያ ኦረንቴሽን እየሰጡ ነው።
----------------------------------------
ዩኒቨርስቲዎች የ12ኛ ክፍል ፈተና ለመፈተን ለተመደቡ የፈተና ጣቢያ ኃላፊዎች፣ ለሱፐርቫይዘሮች፣ ለፈታኞች፣ ማየት ለተሳናቸው ተፈታኝ አንባቢዎችና ለመልስ ወረቀት ቆጣሪዎች ኦሬንቴሽን እየሰጡ ነው።

ዩኒቨርስቲዎቹ በተመሳሳይ ለተፈታኝ ተማሪዎችም ስለ ፈተና ሰርዓቱ ኦረንቴሽን በመስጠት ላይ ናቸው።

የመጀመሪያ ዙር የ12ኛ ክፍል ፈተና ተፈታኞች ከመስከረም 26 ጀምሮ ወደየተመደቡበት ዩኒቨርስቲ ሲገቡ መቆየታቸው ይታወሳል።

የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከነገ ጀምሮ የሚሰጥ ይሆናል።

ምስል - የወለጋ,ቡሌሆራ እና የወልድያ ዩኒቨርስቲ
911 views14:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-09 17:25:43
ወልድያ ዩኒቨርስቲ በፈተናው አተገባበር ዙርያ ኦሬንቴሽን ሰጥቷል።
-------------------

ወልድያ ዩኒቨርሲቲ ለተመደቡ የፈተና ጣቢያ ኃላፊዎች፣ ለሱፐርቫይዘሮች፣ ለፈታኞች፣ ማየት ለተሳናቸው ተፈታኝ አንባቢዎችና ለመልስ ወረቀት ቆጣሪዎች ኦሬንቴሽን ተሰጥቷል።

በኦሬንቴሽኑ ላይ የወልድያ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር አበበ ግርማን ጨምሮ ከትምህርት ሚኒስቴርና ከፈተናዎች አገልግሎት ተመድበው የመጡና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላትም ተገኝተዋል።

የወልድያ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር አበበ ግርማ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት በማስተላለፍ እንደሃገር የተሰጠንን ሃላፊነት በአግባቡ ለመወጣት በብዙ ችግርና ጭንቀት ውስጥ ሁነን እስከዚህ ድረስ ያለውን ምዕራፍ በተሳካ ሁኔታ ለመስራት ችለናል ብለዋል።

በቀጣይ በጋራ በመስራት ፈተናው በሰላምና በተሳካ ሁኔታ ለማጠናቀቅ ሁላችንም የተሰጠንን ኃላፊነትና ተግባር በአግባቡ ልንወጣ ይገባናል ሲሉ አሳስበዋል።

የእያንዳንዱ ተግባርና ኃላፊነት ምን እንደሆነ በፈተናው ማዕከል አስተባባሪ ዶ/ር ሽመልስ ሳህሉ አማካኝነት ለተሳታፊዎች ገለጻ ተደርጓል።
750 views14:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-08 17:11:52
በቡሌ ሆራ ዩኒቨርስቲ የ12ኛ ክፍል ተፈታኟ መንታ ልጆችን ተገላገለች
--------------------------------------

የ12ኛ ክፍል ፈተናል ለመውሰድ ወደ ቡሌ ሆራ ዩኒቨርስቲ የገባቸው ተማሪ መንታ ልጆችን ተገላገለች።

በአሁኑ ሰዓት እናት እና መንታ ልጆቿ በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ ተገልጿል።

ከዚህ በተጨማሪም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ለመውሰድ በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ከተመደቡት ተማሪዎች መካከል ሦስት ተፈታኞች ለፈተና በሔዱባቸው ዩኒቨርስቲዎች ልጆቻቸውን በሰላም ተገላግለዋል።

ተማሪዎቹ በ ደብረ ማርቆስ፣ አምቦ እና ድሬደዋ ዩኒቨርስቲ ለፈተና በሄዱበት በሰላም መገላገላቸው ተገልጿል።
570 views14:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-08 17:11:51
የአሶሳ ዩኒቨርስቲ ዝግጅቱን በማጠናቀቅ ተፈተኛ ተማሪዎችን እየተቀበለ ይገኛል
---------------------------------------------------

የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች በአሶሳ ዩኒቨርስቲ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የፈተና አሰጣጥ ዝግጅት ምልከታ አካሂደዋል።

በዩኒቨርስቲው የተማሪዎች አቀባበል ሁኔታ ፣ የመፈተኛ ክፍሎች ዝግጅት እና በደህንነትን ለማስጠበቅ የተሰሩ ስራዎችንም ተመልክተዋል።

የአሶሳ ዩኒቨርስቲ ፕሬዘዳንት ከማል አብዱረሂም (ዶ/ር) ዩኒቨርስቲው ትምህርት ሚኒስቴር በዘረጋው አሰራርና መመሪያ መሰረት ዩኒቨርስቲያቸው ዝግጅቱን በማጠናቀቅ ተማሪዎችን እየተቀበለ መሆኑን ተናግረዋል።

ዩኒቨርስቲው በግልገል በለስ መምህራን ትምህርት ማስልጠኛ ኮሌጅና በፓዊ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ተፈታኞችን እየተቀበለ ይገኛል።

በአሶሳ ዩኒቨርስቲ 10,021 ተማሪዎች በሁለቱም የትምህርት መስኮች የ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተናን ይወስዳሉ።

ምንጭ:- የቤኒሻንጉል ክልል ትምህርት ቢሮ
475 views14:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-08 17:11:51
በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርስቲ ከ 90 በመቶ በላይ የሚሆኑት ተፈታኞች ዩኒቨርስቲ ገብተዋል።
-------------------

የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርስቲ የ2014ዓም የ12ኛ ክፍል 37,000 ተፈታኝ ተማሪዎች የሚቀበል ሲሆን ከ 90 በመቶ በላይ የሚሆኑት ዩኒቨርስቲ ገብተዋል።

የዩኒቨርስቲው ፕሬዚዳንት ዶክተር ታፈረ መላኩ እንደገለፁት ዩኒቨርስቲው መስከረም 30 ለሚጀመረው ማህበራዊ ሳይንስ ፈተና ዝግጅት አጠናቋል።

ዩኒቨርስቲ ው ለፈተናው የሚመጡ ተማሪዎች የሚገለገሉባቸውን የማደሪያ የመመገቢያ ና የመፈተኛ ክፍሎች በበቂ ሁኔታ ማሟላቱን ፕሬዚዳንቱ ጠቁመዋል።
386 views14:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-08 17:11:50
ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኞች አቀባበልን ተመለከቱ
--------------------------

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመገኘት ዩኒቨርስቲው ለ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ያደረገውን ዝግጅት እና አቀባበል ተመልክተዋል።

ሚኒስትሩ በጉብኝታቸውም ለፈተና መግባት የጀመሩ የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎችን አግኝተው አነጋግረዋል፡፡

የመጀመሪያ ዙር የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች ከመስከረም 26 ጀምሮ ወደ ሚፈተኑበት ዩኒቨርስቲዎች እየገቡ ይገኛሉ።

በነገው እለትም ለተፈታኝ ተማሪዎች ኦረንቴሽን የሚሰጥ ይሆናል።
348 views14:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-08 17:11:50
ወራቤ ዪኒቨርሲቲ የ12ኛ ክፍል የማህበራዊ ሳይንስ የመጀመሪያ ዙር ተፈታኝ ተማሪዎችን እየተቀበለ ይገኛል።
------------------------------------
ወራቤ ዩኒቨርስቲ  በመጀመሪያ ዙር የሚፈተኑ ከ8400 በለይ የሚሆኑ የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎችን ከትላንት ጀምሮ እየተቀበለ ይገኛል።

የዩኒቨርስቲው አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዚዳንት  ዶ/ር መሃመድ  አወል  ዩኒቨርሲቲው ተማሪዎቹን ለመፈተን የሚያስችለውን ቅድመ ዝግጅት አጠናቆ ተፈታኞቹን እየተቀበለ ይገኛል ብለዋል።

በዛሬው እለትም ለፈታኞች፣ ለሱፐር ቫይዘሮችና ለፈተና ጣቢያ ኃላፊዎች በፈተና አሰጣጥ ሂደት በተፈቀዱና በተከለከሉ ጉዳዮች ላይ ኦረንቴሽን እንደሚሰጣቸው ገልጸዋል ።

ፈተናውን ሁሉም አስፈፃሚ ህጉን ተከትሎ እንዲሰጥ በማድረግ  እንደ ዩኒቨርሲቲ በተቻለ መጠን ከግድፈት ነፃ እንዲሆን የሚቻለውን ሁሉ እንደሚያደርጉ ገልፀዋል ።

ዩኒቨርሲቲዎች የ2014ዓ.ም የ12ኛ ክፍል የመጀመሪያ ዙር ተፈታኝ ተማሪዎችን ከመስከረም 26/2015 ጀምሮ እየተቀበሉ እንደሚገኙ ይታወቃል።
338 views14:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-08 17:11:50
የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ባሉት ሶስት ካምፓሶች  የ12ኛ ክፍል ተፈታኞችን እየተቀበለ ነው።

ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የ12ኛ ክፍል የመጀመሪያ ዙር የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ፈተና የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኝ ተማሪዎችን እየተቀበለ ይገኛል።

ዩኒቨርሲተው በሉት ሶስት ካምፓሶች ተማሪዎቹን ለመቀበል የሚያስችለውን ቅድመ ዝግጅት አጠናቆ የመጀመሪያ ዙር የማህበራዊ ሳይንስ ተፈተኞችን እየተቀበለ እንደሚገኝ የዩኒቨርስቲው ኘሬዜዳንት ሀብታሙ አበበ (ዶ/ር) ገልፀዋል ።

ኘሬዚዳንቱ በመጀመሪያ ዙር በዋቸሞ ካምፓስ 18876፣ በዱራሜ ካምፓስ 2086 እንዲሁም ንግስት ኢሌኒ ካምፓስ ደግሞ 450 ተፈታኝ ተማሪዎችን እንደሚቀበል ገልፀዋል።

በዛሬው እለትም ለፈታኝ መምህራን፣ ለሱፐር ቫይዘሮች እንዲሁም ለፈተና ጣቢያ ኃላፊዎች ኦሬንቴሽን እንደሚሰጥ የገለፁ ሲሆን ለአጠቃላይ ተፈታኝ ተማሪዎችም  በነገው እለት ኦሬንቴሽን እንደሚሰጣቸው ገልፀዋል።

ወደ ዩኒቨርሲቲው እየገቡ ያሉ ተማሪዎች በበኩላቸው  በዩኒቨርስቲው የተደረገላቸው አቀባበል ጥሩ መሆኑን ገልፀው   ፈናውን ለመውሰድ ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።

የ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል የመጀመሪያ ዙር ፈተና ከመስከረም 30/2015ዓ.ም ጀምሮ እንደሚሰጥ ይታወቃል።
345 views14:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ