አደጋ ላይ የጣለህ ስለማይወድህ ሳይሆን ልብህን እንድትሰጠው ፈልጎ ነው::በፍቅር እምቢ ስትለው በመከራ ከሰማኸኝ ብሎ ነው:: - "የእርጅና ወራት ሳይመጣ በጉብዝና ወራት ፈጣሪህን አስብ!" የተባልከው እውነት ነው:: - በፍቅር አምላክህን ካላሰብከው በህመም ታስበዋለህ:: - ነፃ በሆንክ ሰዓት ያልጠራኸውን በእስር ስትወድቅ ተጠራለህ:: - በጤና ያፈለከውን ስትታመም ትፈልጋለህ::በሰላም ያላዋራኸን አዳጋ ሲያጋጥምህ ታዋራለህ:: - ሰዓቱ ደርሷል::አሁንም የመዳንህን እድል አታባክነው::በምድር ቅዠት ተኝተህ የአምላክህን መንግስት አትለፈው:: - ምድር እንደሆነች ከጊዚያዊ እርካታ ውጪ የምትሰጥህ አንዳች የላትም::የሰጠችህንም ነገር አንድ በአንድ ቆጥራ ስትሞት ትቀበልሃለች:: - ማንም ሰው ሊነጥቅህ የማይቻለውን መንፈስህን ብቻ ፈልገው::ነፃ የምትወጣው በእርሱ ነው:: - አምላክህን ብትውደው ጊዜ እና ትኩረትህን በሰጠኸው ነበር::ድምፁን ለመስማት እና የአብሮነት ጊዜን ለማሳለፍ በተመኘህ ነበረ:: - ነገሩ የማያውቁት አገር አይናፍቅም ሆኖል::በአለም አስትዳደግ አምላክህን እንድትረሳ ተደርጏል::ጠረኑ: ደግንቱ: ውበቱ: እርዳታው እና ቸርነቱ ጠፍቶሃል::አለም አታልሎህ ውስዶሃል:: - እርሱ ግን ይወድሃል እና መቼም አይተውህም::ብትጠላው አይጠላህም::ህጉን ብታፈርስም አያፈርስህም:: - ጠባዩ ሙሉ ፍቅር ነውና እስከ መጨረሻው ያፈቅርሃል::በፍቅር ካልሰማኸው በህመም ቢሆን እንድትቀርበው ይስብሃል:: - አደጋ ላይ የጣለህ ስለማይወድህ ሳይሆን ልብህን እንድትሰጠው ፈልጎ ነው::በፍቅር እምቢ ስትለው በመከራ ከሰማኸኝ ብሎ ነው:: - እስቲ ደስስስ ይበለው ስማው::ልብህን ወደ እርሱ መልስ::የቀድመ የአባት እና የልጅ ፍቅራችሁን አድስ::እስቲ አንተ በትራህ አምላክህን ደስስስስ አሰኘው::ልቡን አብራላት::የፍቅር: የይቅርታ እና የሰላም ሰው ሁንለት:: - 148 views ☞net, 16:54