2024-04-26 10:01:59
"ጥፋት እንጅ ክህደት በአማራ ህዝብ ላይ አንፈጽምም"።
ምስራቅ አማራ ፋኖ ዕዝ
17/08/2016
ከሃያ አምስት በላይ የአድማ ብትና አባላት የምስራቅ አማራ ፋኖ ዕዝ አሳምነው ጽጌ ክፍለ ጦርን ተቀላቅለዋል።ከተቀላቀሉ በኋላም እኛ እውነት ነው አማራ ህዝብ ዘንድ ጥፋት አጥፍተናል ነገር ግን ክህደት አልፈጸምንም።
ከነገ ዛሬ ይለውጣል ብለን በተለይ የአማራ የወሰን ጥያቄዎችን ያስከብራል ብሎም ከአማራ ህዝብ ጎን ይቆማል ያለው የብልጽግና አመራር ራሱን ለሆዱ ሽቶ መሬቱም ለዳግም ወረራ ዳርጎ የአማራን ህዝብ ዳግም ለባርነት አሳልፎ ሊሰጥ እንደሆነ ዘግይተን ብንረዳም ዛሬ ግን ከተከበረው የአማራ ፋኖ ጋር ተቀላቅለናል።
ወደፊትም የትኛውንም ግዳጅ ለመወጣት ዝግጁ መሆናችንን መላው የአማራ ህዝብ ሊረዳልን ይገባል ብለዋል።
በተደጋጋሚ የወራሪው ስርአት ዙፋን ጠባቂዎችም ከቀን ወደ ቀን ወደ ፋኖ እየተቀላቀሉና ግዳጅ እየፈጸሙ ይገኛሉ።
በደቡብ ወሎና በሰሜን ወሎ ዞን የሚንቀሳቀሰው የምስራቅ አማራ ፋኖ ዕዝ ከሁሉም በተለዬ መልኩ የአንድነቱን ጉዳይ አበክሮ እየሰራና ጥሩ ሂደት ላይ መሆኑን አብክሮ መግለጽ ይፈልጋል።
ጓዶች የሞቱለትን አላማ ከግብ እናደርሳለን!!
ምስራቅ አማራ ፋኖ
12.4K viewsedited 07:01