Get Mystery Box with random crypto!

@newayekidisat @newayekidisat #በሰሙነ_ሕማማት_የሚገኙ_ዕለታትና_ስያሜአቸው ዕ | ንዋየ ቅድሳት

@newayekidisat
@newayekidisat

#በሰሙነ_ሕማማት_የሚገኙ_ዕለታትና_ስያሜአቸው

ዕለተ ሐሙስ

ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ
ክርስቶስ በዚህ ዕለት ፍጹም ሰው፤ ፍጹም
አምላክ መኾኑን ለመግለጥ እና ለአርአያነት
ሲጸልይ በማደሩ ምክንያት ዕለቱ ‹ጸሎተ
ሐሙስ› በመባል ይታወቃል፡፡ @newayekidisat
ትሕትናንና
ፍቅርን እንደዚሁም የአገልግሎትን ትርጕም
ለማስረዳትና ለማስገንዘብ ጌታችን የደቀ
መዛሙርቱን እግር በማጠቡ ዕለቱ ‹ሕጽበተ
ሐሙስ› በመባልም ይጠራል፡፡ ጌታችን የደቀ
መዛሙርቱን እግር ባጠበ ጊዜም፡- «…
ያደረግሁላችሁን ታስተውሉታላችሁን?…
እንግዲህ እኔ ጌታና መምህር ስኾን
እግራችሁን ካጠብሁ እናንተ ደግሞ እርስ
በእርሳችሁ ትተጣጠቡ ዘንድ ይገባችኋል፤››
በማለት የእርሱን አርአያነት መከተል
እንደሚገባ አስተምሯል (ዮሐ. ፲፫፥፲፪-፳)፡፡ @newayekidisat
ዕለተ ሐሙስ ጌታችን ‹‹… ይህ ስለ እናንተ
በመስቀል ላይ የሚቈረሰው ሥጋዬ ነው፤
እንካችሁ ብሉ፡፡ ይህ ስለ እናንተ የሚፈስ
ደሜ ነው፤ ከእርሱ ጠጡ፤›› በማለት
ምሥጢረ ቍርባንን የመሠረተበት
የጀመረበት ቀን በመኾኑ ‹የምሥጢር ቀን›
ተብሎም ይጠራል (ማቴ. ፳፮፥፳፮-፳፱)፡፡ @newayekidisat
ይኸውም ምእመናን ሥጋውንና ደሙን
ተቀብለን ከእርሱ ጋር አንድነትና ኅብረት
እንዲኖረን፤ ጥንተ ጠላት ዲለብሎስንም
ፍጹም ድል ነሥተን ሰማያዊት ርስት
መንግሥተ ሰማያትን እንድንወርስ ለማስቻል
ነው፡፡ አይሁድ ጌታችንን የያዙበት ቀን ስለ
ኾነ በዚህ ዕለት በለኆሣሥ (ብዙ የድምፅ
ጩኸት ሳይሰማ) የቅዳሴ ሥርዓት
ይፈጸማል፡፡ @newayekidisat መላው ሕዝበ ክርስቲያን
የሕጽበት፣ የምሥጢር፣ የጸሎት ቀን
በተባለው በዚህ ዕለት በንስሐ ታጥበው፣
ሥጋ ወደሙ እንዲቀበሉ ቤተ ክርስቲያን
በአጽንዖት ታስተምራለች፡፡

#forward በማድረግ ለወዳጆ ያጋሩ
@newayekidisat
@newayekidisat