ኪዳነምህረት እመቤት /2/ ነይልን ነይልን ካለንበት /2/ እዝ...... ከሰማያት በላይ ካለው ከማደርያሽ /2/ ዝማሬ ከሞልው ከዘላለም ቤትሽ የምድር ፍጥረታት ማርያም ማርያም ሲሉሽ የቃል እናት እመቤቴ ነይ በሰረገላ /2/ እዝ............ ከፀጥታ ወደብ ከፍቅር አውድማ /2/ ከሰላሙን መንደር ከእውነት ከተማ ሳሊለነ ቅድስት ውዳሴሽ ሲሰማ /2/ ከሚካኤል ከገብርኤል ጋር ነይልን ከራማ /2/ እዝ............... ዘርፋፋው ቀሚስሽ ይወረደ ከሰማያት /2/ እንባችን ይታበስ በአንቺ አማላጅነት የፅዮን ዝማሬ ተሞላች ነፍሳችን /2/ ነይ ነይ ነይ እንበል እንደአባቶቻችን /2/ እዝ................... ፍጥረታት ቢድኑ በአማላጅነትሽ /2/ የዘላለም ኪዳን አማኑኤል ሰጠሽ ትውልድ ይህን አምኖ ንፅህት ይልሻል /2/ እናቴ መመክያዬ ምርኩዜ ሆነሻል/2/ እዝ................ የልብን ሲያዋዩሽ ሰምተሽ ዝም አትይም /2/ ችግረኛን አይቶ ልብሽ አይጨክንም ከአይን ጥቅሻ ፈጥነሽ ትደርሽለታለሽ /2/ ከሀዘን ከመከራ ታሳሪፊዋለሽ /2/ 37 viewsTesfanesh Seyoum(YSimoen), 05:51