Get Mystery Box with random crypto!

STUDENTS NEWS CHANNEL (የተማሪዎች ዜና መስኮት)

የሰርጥ አድራሻ: @nationalexamsresult
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች: 40.95K
የሰርጥ መግለጫ

የተማሪ እና ተማሪ ነክ መረጃዎች ይቀርቡበታል፡

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2024-03-16 15:17:00
ማስጠንቀቂያው በተለያዩ ጊቢዎች ቀጥሏል ትናንትና ማታ ከንግድ ባንክ የሌላችሁን ብር ለወሰዳችሁ ተማሪዎች በሙሉ

AASTU

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT
12.6K views12:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-02-13 15:48:48
ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የነባር የ1ኛ ዓመት 2ኛ ሴሚስተር ተማሪዎች እንዲሁም የ3ኛ ዓመትና ከዚያ በላይ ተማሪዎች የመጨረሻ ምዝገባ ቀን ዓርብ የካቲት 08/2016 ዓ.ም መሆኑን ገልጿል።

ከተጠቀሰው ቀን በኋላ ምዝገባ ኦንደማይኖር ዩኒቨርሲቲው አሳስቧል።

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
13.1K viewsedited  12:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-02-13 06:21:56 #repost

የመውጫ ፈተና ከረቡዕ ጀምሮ መሰጠት ይጀምራል።

በዚህ ፈተና ወቅት ከተማሪዎች እና ከፈታኞች ምን እጠበቃል ?

[ ከተፈታኞች የሚጠበቅ ]

- ተፈታኞች ወደ መፈተኛ ክፍላቸው ሲመጡ ማንኛውም አይነት ስልክ፣ ስማርት ሰዓት ፣ ታብሌት ፣ ላፕቶፕና ... ወዘተ ተመሳሳይ ኤክትሮኒክ ቁሳቁስ መያዝ በፍፁም የተከለከለ ነው።  (ይዞ የተገኘ ፈተናው /ውጤቱ ተሰርዞበት በቀጣይ ጊዜ እንዲቀመጥ ይደርጋል)

- ፈተና ከመጀመሩ ከ30 ደቂቃ በፊት መፈተኛ ክፍል መገኘት አለባቸው።

- ተፈታኞች ለፈተና ሲመጡ ID መያዝ ያለባቸው ሲሆን User Name እና Password lower-case and upper-case ፊደላትን ለይተው በጥንቃቄ መያዝ አለባቸው።

- ተፈታኞች ፈተና ከተጀመረ በኃላ ከ30 ደቂቃ በፊት ከፈተናው ክፍል መውጣት የለባቸውም።

- ተፈታኞች ፤ ፈተናውን የሚያስፈትኑ መምህራን በሚያሳዩት ቦታ ብቻ መቀመጥ አለባቸው።

- ሁሉም ተፈታኝ እንዲቀመጥ የተመደበበት የራሱ ኮምፒውተር ላይ ብቻ ተቀምጦ መክፈትና መጠቀም አለበት።

- በፈተና ክፍል ውስጥ መነጋገርም ሆነ ከቦታ ቦታ መዘዋወር በፍፁም የተከለከለ ነው። እንዲሁም ማንኛውም ተፈታኝ ከጎኑ ያለውን ተማሪ ኮምፒውተር በፍፁም ማየት የለበትም።

- ምንም ዓይነት ወረቀት ወደ መፈተኛ ክፍል ይዞ መምጣት አይቻልም።

- ተፈታኞች በምንም አይነት ሁኔታ መኮርጅም ሆነ ማስኮርጅ ተግባር ላይ ቢሳተፉ እርምጃ ይወሰድባቸዋል።

- ሁሉም ተፈታኝ ተማሪዎች ለፈተናው ፈታኝ መምህራን እና ለአስተባባሪዎች መታዘዝ ያለባቸው ሲሆን የፈተናው ደንብና ስርዓት ተገዢ መሆን ይጠበቅባቸዋል።

NB. ሁሉም ተፈታኞች ወደ ፈተና መፈተኛ ክፍል ተፈትሸው እንዲገቡ የሚደረግ ሲሆን ማንኛውም ተፈታኝ ከፀጥታ ኃይሉ ጋር በፍተሻ ወቅት ይሁን ሥርዓት ለማስያዝ በሚደረግ እንቅስቃሴ እንቅፋት ሆኖ ከተገኘ ከመፈተኛ አከባቢ እንዲገለል ተደርጎ በቀጣዩ የመውጫ ፈተና መስጫ ወቅት እንዲቀመጥ ይፈቀድለታል።

[ ከፈታኝ መምህራን የሚጠበቅ ]

- የተፈታኝ ተማሪዎችን ID በአግባቡ በማረጋገጥ ወደ ክፍል እንዲገቡ ማደረግ ይጠበቅባቸዋል።

- ተፈታኝ ተማሪዎችን በሥም ዝርዝራቸው መሠረት ማስቀመጥ ይኖርባቸዋል።

- ፈታኝ መምራህን የተፈታኝ ተማሪዎችን አቴንዳንሰ ይወስዳሉ ፤ ተማሪዎችን ፊርማ ያስፈርማሉ።

- በፈተና ክፍል ውስጥ ደምጽ እንዳይሰማ፣ ተማሪዎች ከቦታ ቦታ እንዳይዘዋወሩ ተገቢውን ቁጥጥር ማድረግ አለባቸው።

- የፈተናው አጠቃለይ ሂደት በትኩረት መከታተል አለባቸው።

- በህመም ምክንያት ተማሪዎች ከመተኛ ክፍል መውጣት ቢፈልጉ ከሱፐርቨዘር ጋር በመነጋገር አስፈላጊውን እርዳታ ያደርጋሉ።

- ተማሪዎች በጎናቸው ያለውን ሌላ ኮምፒውተር እንዳይመለከቱ መቆጣጠር አለባቸው።

- ተማሪዎች ፈተናው ከተጀመረ ከ30 ደቂቃ በፊት እንዳይወጡ መቆጣጠር ይጠበቅባቸዋል።

- ሲኮርጅ ወይም ሲያስኮርጅ የተገኘ ማንኛውም ተማሪ ከመፈተኛ ክፍል እንዲወጣ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል።

- ፈተናው ከጀመረ ከ15 ደቂቃ በኃላ የሚመጣ ተማሪ እንዲገባ ማድረግ የላባቸውም።

- የፈተና አፈጻጸም ሪፖርት ለሱፐርቨዘር ማቅረብ ይጠብቅባቸዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ነው የሰበሰበው።

ለመላው ተፈታኞች መልካም ፈተና ይሆን ዘንድ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይመኛል !

(መልዕክቱ በባለፈው ዓመት የፈተና ወቅት የተዘጋጀ እና በቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ላይ የተለጠፈ ነው)

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
13.1K views03:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-02-08 19:57:28 የሁለተኛ ወሰነ ትምህርት የካቲት 4/2016 ዓ.ም ይጀምራል፡፡

(ቀን ጥር 30/2016 ዓ.ም)

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሁለተኛ ወሰነ ትምህርት የካቲት 4/2016 ዓ.ም የሚጀምር መሆኑን እናሳውቃለን፡፡

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
13.2K views16:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-02-08 08:45:53
#ማስታወቂያ

ለድጋሚ (Re-exam) ተፈታኞች በሙሉ

የካቲት 6/2016 ዓ.ም ጀምሮ የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና  ለመፈተን በመጠባበቅ ላይ ለምትገኙ የ ድጋሚ (Re-exam) ተፈታኞች በሙሉ የመፈታኛ የይለፍቃል (Password) ከታች በተዘረዘሩት አማራጮች ማግኘት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

1. በምዝገባ ወቅት በሞላችሁት email በኩል

2.  https://exam.ethernet.edu.et  ላይ በመግባት የከፈላችሁበትን Transaction Number በማስገባት እንዲሁም

3. ከተመደባብችሁብት የመፈተኛ ተቋም ማግኘት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

ማሳሰቢያ
• ለመጀመሪያ ጊዜ የመዉጫ ፈተና የምትፈተኑ እጩ ተመራቂዎች የይለፍቃል (Password) የምታገኙት ከምትማሩበት ወይም ከተመደባብችሁበት የመፈተኛ ተቋም ብቻ መሆኑን እናሳውቃለን።

• ሁሉም ተፈታኞች የሞዴል ፈተናን እስከ  የካቲት 5/2016 ዓ.ም መውሰድ ይኖርባቸዋል።

ትምህርት ሚኒስቴር

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
14.2K viewsedited  05:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-01-31 21:38:02 #Update

የ2016 ዓ.ም አጋማሽ ዓመት የመውጫ ፈተና የሚሰጥበት ጊዜ ተራዝሟል።

የመውጫ ፈተናው ከጥር 27 እስከ የካቲት 01/2016 ዓ.ም ይሰጣል ተብሎ እንደነበር አይዘነጋም።

ትምህርት ሚኒስቴር አዲስ ይፋ ባደረገው መርሐግብር ፈተናው ከየካቲት 06 እስከ 09/2016 ዓ.ም እንደሚሰጥ ታውቋል።

ለአዲስ ተፈታኞች ሞዴል ፈተና ከጥር 27 እስከ 30/2016 ዓ.ም እንደሚሰጥ ቲክቫህ ከትምህርት ሚኒስቴር ያገኘው መረጃ ያሳያል።

የተፈታኞች ዝርዝር ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ በቀጣይ ቀናት እንደሚላክም ተገልጿል።

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
13.0K viewsedited  18:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-12-19 19:33:28
ለጥናትና ምርምርዎ እገዛ ይፈልጋሉ?
    አዎ ከሆነ መልስዎ!
በመንግስትም ሆነ በግል ዩኒቨርሲቲ/ኮሌጅ በዲፕሎማ፣ዲግሪ እና በማስተርስ ፕሮግራም ለምትማሩ እና ትምህርታችሁን ጨርሳችሁ የምርቃት ጊዜያችሁን በጉጉት ለምትጠብቁ ሁሉ ስለ ጥናትና ምርምር በቂ እዉቀትን በመያዝ የመመረቂያ ፅሁፋችሁን ተመራጭ እና ተወዳጅ አድርጋችሁ በመስራት በጥሩ ዉጤት ትመረቁ  ዘንድ እናግዝዎታለን፡

If you need support related to:    
1 Assignment / አሳይመንት
2 Research / ሪሰርች
3 Proposal / ፕሮፖዛል
4 Term Paper /  ተረም ፔፐር
5 Case study/ ኬዝ ስተዲ
6 Article Review
7  Mini research
8  Business plan
9  Environmental impact assessment [EIA]

Any other Questions
Contact us via
@ResearcherETH
@ResearcherETH
@ResearcherETH
12.6K viewsedited  16:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-12-12 12:25:48
አዲግራት ዩኒቨርስቲ በትምህርት ሚኒስቴር የተመደቡለትን 832 አዲስ ተማሪዎች መቀበሉን አስታወቀ።

ዩኒቨርስቲው በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን ከ1 ሺሕ 500 በላይ ተማሪዎች ታህሳስ 6 ቀን 2016 ዓ.ም እንደሚያስመረቅም ተመላክቷል።

የዩኒቨርስቲው የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር ዮሐንስ ከበደ እንዳሉት ዩኒቨርሲቲው ተማሪዎቹን የተቀበለው የመመገቢያ፣ የመማሪያ፣ የመኝታ እና ሌሎች ለመማር ማስተማር ሥራው አስፈላጊ የሆኑ የዝግጅት ሥራዎችን ካጠናቀቀ በኋላ መሆኑን ተናግረዋል።

ከዚህ በተጨማሪ የዩኒቨርስቲውን ቅጥር ግቢ በማስዋብና በማፅዳት ተማሪዎቹን መቀበሉን ዳይሬክተሩ ገልጸዋል።

ዩኒቨርስቲው ትምህርታቸውን በተለያዩ ምክንያቶች አቋርጠው ከነበሩ ከ5 ሺሕ በላይ ተማሪዎች መካከል ዳግም ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ 1 ሺሕ 500 ተማሪዎችን የፊታችን ቅዳሜ እንደሚያስመርቅም ዮሐንስ አመልክተዋል።

የመቀሌ እና የአክሱም ዩኒቨርስቲዎች በተያዘው የትምህርት ዘመን የሚያስተምሯቸውን ከ2 ሺሕ በላይ ተማሪዎች ባለፈው ሳምንት መቀበላቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
12.7K viewsedited  09:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-12-09 12:47:13
የኢትዮጵያ አየርመንገድ አቪዬሽን ዩንቨርስቲ ከ600 በላይ በተለያዩ መስኮች ያስለጠናቸውን ተማሪዎችን በማስመረቅ ላይ ይገኛል።

በዛሬው የምርቃት ፕሮግራም በአውሮፕላን አብራሪነት በአውሮፕላን ጥገና እና መስተንግዶ ያሰለጠናቸውን ተማሪዎችን ነው እያስመረቀ የሚገኘው።

በምርቃት ስነስርዓቱ የኢትዮጵያ አየርመንገድ ዋና ስር አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰውን ጨምሮ የኢትዮጵያ አቪዬሽን ዩንቨርስቲ ፕሬዚዳንት አቶ ካሴ ይማም የተማሪዎች ወላጆች በተገኙበት በኢትዮጵያ አየርመንገድ ውስጥ ፕሮግራሙ እየተካሄደ ይገኛል።

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
12.6K views09:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-11-16 20:12:16
በአማራ ክልል በጸጥታ ችግር ምክንያት የባከነውን የትምህርት ጊዜ ለማካካስ የዓመቱን የመማር ማስተማር ሒደት ለማሻሻል ጥናት እየተደረገ መሆኑ ተገለጸ፡፡

በክልሉ ምስራቅ፣ ምዕራብ እና ሰሜን ጎጃም ዞኖች እስካሁን ትምህርት አለመጀመሩን የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ሙሉነሽ ደሴ (ዶ/ር) ለአሚኮ ተናግረዋል። 

በጸጥታ ሥጋት ምክንያት ከተገለፁት ዞኖች ውጭ በሚገኙ የክልሉ አካባቢዎች 60 በመቶ የአንደኛ ደረጃ እና 55 በመቶ የ2ኛ ደረጃ ተማሪዎች ብቻ በመማር ላይ እንደሚገኙ ገልጸዋል፡፡

በክልሉ በየጊዜው ሰላም በሚኾንባቸው አካባቢዎች ከጸጥታ መዋቅሩ እና ከማኅበረሰቡ ጋር በመቀናጀት ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታ እንዲመለሱ እየተሠራ ነው ብለዋል።

የባከነውን የትምህርት ጊዜ ለማካካስ ቢሮው የዓመቱን የትምህርት ሥርዓት እንደገና ለማሻሻል ጥናት እያደረገ  እንደሚገኝም ኃላፊዋ ጠቁመዋል።

በተለይ በዚህ ዓመት የክልል እና ሀገር አቀፍ ፈተና ለሚወስዱ የ6ኛ፣ የ8ኛ እና የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የባከኑ ጊዜያትን በልዩ ሁኔታ ለመሸፈን ከመምህራን እና ርዕሰ መምህራን ጋር ውይይት እየተደረገ መኾኑን ገልጸዋል፡፡

አሚኮ

⊰  ㅤ    ⫹⫺ㅤ     ⎙ㅤ     ⌲ ⊱
࿙ ᴸⁱᵏᵉ    ˢᵘᵖᵖᵒʳᵗ    ˢᵃᵛᵉ     ˢʰᵃʳᵉ ࿚

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT
13.2K viewsedited  17:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ