Get Mystery Box with random crypto!

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ National Election Board of Ethiopia

የቴሌግራም ቻናል አርማ nationalelectionboardnebe — የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ National Election Board of Ethiopia
የሰርጥ አድራሻ: @nationalelectionboardnebe
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 23.27K
የሰርጥ መግለጫ

NEBE

Ratings & Reviews

3.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2024-05-12 09:36:46
የመራጮች ምዝገባ መራዘሙን ስለማሳወቅ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በ6ኛው ዙር ጠቅላላ ምርጫ ቀሪ ምርጫ በሚደረግባቸው የቤኒሻንጉል ጉሙዝ እና አፋር ክልሎች እንዲሁም ድጋሚ ምርጫ በሚደረግባቸው በጅግጅጋ 2 እና መስቃንና ማረቆ ምርጫ ክልሎች ሰኔ 9 ቀን 2016 ዓ.ም. ምርጫ ለማከናወን የተለያዩ ዝግጅቶችን በማድረግ ላይ ይገኛል።

ቦርዱ ከሚያዝያ 21 እስከ ግንቦት 5 ቀን 2016 ዓ.ም. የጊዜ ሰሌዳ በማውጣት የመራጮች ምዝገባ እያካሄደ ይገኛል። ነገር ግን የመራጮች ምዝገባ በወጣበት የጊዜ ሰሌዳ ወቅት ተደራራቢ የህዝብና የሃይማኖት በዓላት የነበሩ በመሆኑ፣ የመራጮች ምዝገባ የሚደረግባቸው አንዳንድ ምርጫ ጣቢያዎች በወቅቱ ባለመከፈታቸውና በምርጫ የሚወዳደሩት የፓለቲካ ፓርቲዎችም በተመሳሳይ ሁኔታ የመራጮች ምዝገባ ቀን እንዲራዘም በመጠየቃቸው ቦርዱ የመራጮችን የምዝገባ ቀን እስክ ግንቦት 12 ቀን 2016 ዓ.ም. አስረዝሟል።

በመሆኑም ምርጫ በሚካሄድባቸው ምርጫ ክልሉች የሚገኙ መራጮች ይህ የተሰጠውን የመራጮች የምዝገባ ወቅት በመጠቀም ለምዝገባ ብቁ የሚያደርጉ ማስረጃዎችን በመያዝ በየአካባቢያቸው በሚገኙ ምርጫ ጣቢያዎች በመገኘት በመራጭነት እንዲመዘገቡ ቦርዱ ያስታውቃል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
5.8K views06:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-11 11:48:18
የእጩዎች ምዝገባ መራዘሙን ስለማሳወቅ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በ6ኛው ዙር ጠቅላላ ምርጫ ቀሪ ምርጫ በሚደረግባቸው ቤኒሻንጉል ጉሙዝ እና አፋር ክልሎች እንዲሁም ድጋሚ ምርጫ በሚደረግባቸው በጅግጅጋ 2 እና መስቃንና ማረቆ ምርጫ ክልሎች ሰኔ 9 ቀን 2016 ዓ/ም ምርጫ ለማከናወን የተለያዩ ዝግጅቶችን በማድረግ ላይ ይገኛል።

ቦርዱ የእጩዎች ምዝገባ ከሚያዝያ 21 እስከ ሚያዝያ 30 ቀን 2016 ዓ/ም የጊዜ ሰሌዳ በማውጣት በምርጫው መወዳደር የፈለጉ ዕጩዎች ምዝገባ አካሂዷል:: ነገር ግን የተወሰኑ የፖለቲካ ፓርቲዎች በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ዕጩዎቻቸውን በተለያዩ ምክንያቶች ማስመዝገብ አለመቻላቸውን በመጥቀስ ለእጩዎች ምዝገባ ተጨማሪ ጊዜ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል።

በዚሁ መሰረት ቦርዱ የፖለቲካ ፓርቲዎችን ጥያቄ በመቀበል የእጩዎችን የምዝገባ ጊዜ እስከ ግንቦት 6 ቀን 2016 ዓ/ም አራዝሟል። በመሆኑም የፖለቲካ ፓርቲዎች እና የግል ዕጩ ተወዳደሪዎች በተጠቀሰው የማራዘሚያ ጊዜ በመጠቀም በምትወዳደሩበት ምርጫ ክልል በመቅረብ የሞቱ ወይም በሌላ እጩ የተተኩ የፖለቲካ ፓርቲ አባላትን የመተካት ሂደት በአዋጁ በተቀመጠው ድንጋጌ መሰረት መሆኑን በማረጋገጥና ማስረጃ በማቅረብ ምዝገባውን እንድታከናውኑ ቦርዱ ያስታውቃል ።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
6.4K viewsedited  08:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-10 15:38:41
ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ6ኛው ዙር የጠቅላላ እና የድጋሚ ምርጫ ባልተካሄደባቸው የቤንሻንጉል ጉሙዝ፣ አፋር፣ ሶማሌ እና ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች ሰኔ 9 ቀን 2016 ዓ.ም. የሚካሄደውን ምርጫ መዘገብ ለምትፈልጉ የመገናኛ ብዙኃን የቀረበ ጥሪ

የመገናኛ ብዙኃን ቀጣዩ የ6ኛው ዙር የጠቅላላ እና የድጋሚ ምርጫ ባልተካሄደባቸው የቤንሻንጉል ጉሙዝ፣ አፋር፣ ሶማሌ እና ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች ምርጫው ፍትሐዊ፣ ገለልተኛና ተዓማኒ እንዲሆን የሚያበረክቱት ሚና ከፍተኛ መሆኑን በመገንዘብ፤ የመገናኛ ብዙኃኑና ጋዜጠኞች በምርጫ ጣቢያዎች ተገኝተው ለመዘገብ የሚያስችል የፍቃድ ጥያቄያቸውን ለቦርዱ እንዲያቀርቡ ይህንን ጥሪ ማድረግ አስፈልጓል፡፡ በዚህ መሠረት ለመዘገብ ጥያቄ የሚያቀርቡ የመገናኛ ብዙኃን ...

ዝርዝር መረጃ ለማግኘት እዚህ ማስፈንጠሪያ ላይ ይጫኑ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
6.7K viewsedited  12:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-09 16:55:53 በምርጫ ወቅት በሴቶች ላይ ስለሚፈፀሙ ጥቃቶች በምርጫ ቦርድ ነፃ የስልክ መስመር 778 እና 665 ላይ ጥቆማ ማቅረብ ይችላሉ

Dooro wakti Saymaral yakke bood wagsiisak Dooro Bordih currik yan ta telefoonih nebrol 778 kee 665 haak tascasseenim xiqtaanah

Waxaad kaga warbixin kartaa tacadiyada ka dhanka ah haweenka xiliga doorashada nambarada bilaashka ah ee gudiga doorashada 778 iyo 665
7.9K views13:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-08 12:48:56
የምርጫ ቦርድ የጥሪ ማዕከል አገልግሎት መስጠት ጀመረ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ6ኛው ዙር ሀገራዊ ምርጫ ባልተካሄደባቸው ማዕከላዊ ኢትዮጵያ፣ ሶማሌ፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ እና አፋር ክልሎች ቀሪና የድጋሚ ምርጫ ሰኔ 9 ቀን 2016 ዓ.ም. ለማከናወን በዝግጅት ላይ መሆኑ ይታወቃል።
በዚህም መሰረት ቦርዱ ምርጫ በሚያደርግባቸው አካባቢዎች ለሚፈጠሩ ልዩ ልዩ ሁኔታዎች እና ለመረጃ መለዋወጥ እንዲያገለግል ጊዜያዊ የጥሪ ማዕከል አቋቁማል ስለሆነም ከ6ኛው ዙር ሀገራዊ ቀሪና የድጋሚ ምርጫ ጋር በተያያዘ መረጃ ለማግኘት፤ መረጃ ለመስጠት እና አስፈላጊ የሆኑ ጥቆማዎችን ለምርጫ ቦርድ ለማቅረብ የሚከተሉትን ነፃ የስልክ መስመሮች ይጠቀሙ፡

665 ከቦርዱ ምርጫ አስፈፃሚዎች የሚመጡ ማንኛውም ጥያቄዎች የሚስተናገድበት የውስጥ መረጃ መቀበያ መስመር ነው፡፡

778 ደግሞ ለህዝብ ይፋ የሆነ ሰዎች ወደ ምርጫ ቦርድ በመደወል ቅሬታቸውን የሚያቀርቡበት፤ ጥቆማቸውን የሚሰጡበት እና ሀሳባቸውን የሚገልፁበት መስመር ነው፡፡

ቁጥሮቹ ለደዋዮቹ ነፃ የስልክ መስመሮች ስለሆኑ እና ሁሉንም የስልክ ጥሪ ክፍያዎች የሚከፍለው የምርጫ ቦርድ ስለሆነ የቦርዱ ምርጫ አስፈፃሚዎች በ (665) እና በምርጫው የምትሳተፉ መራጮች፤ ተመራጮች፤ የምርጫ ታዛቢዎች እና ሌሎችም የማህበረሰቡ ክፍሎች በ (778) እየደወላችሁ ያላቹሁን ጥያቄዎች፤ አስተያየቶች፤ ቅሬታዎች እና ጥቆማዎች ለቦርዱ የጥሪ ማዕከሉ ሠራተኞች ማቅረብ ትችላላችሁ፡፡
9.2K views09:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-08 10:41:04
የተለማማጅ ሰራተኛ የቅጥር ማስታወቂያ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሥሩ ለሚገኙ የተለያዩ የሥራ ክፍሎች ተለማማጅ ሰራተኞችን /Internship/ ቀጥሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡ በዚሁም መሠረት ከዚህ በታቸው የተገለፁትን መስፈርቶች የምታሟሉ አመልካቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 5 ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ ከዚህ በታች በተጠቀሰው የስራ ማመልከቻ ማስፈንጠሪያ በመንካት ማመልከት የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡

በማኔጅመንት/ በቢዝነስ አድሚኒስትሬሽን/ በአካውንቲንግና ፋይናንስ/ በኢኮኖሚክስ/ በማርኬቲንግ/ በሕግ/ በኮምፒውተር ሳይንስ/ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ወይም በሌላ ተመሳሳይ የትምህርት ዘርፍ የመጀመሪያ ዲግሪና 0 ዓመት የሥራ ልምድ
በቂ የመግባባት ችሎታ ያላት/ያለው
የተቋሙን ደንብና መመሪያ የምታከብር/ የሚያከብር
ማንኛውም የፖለቲካ ፓርቲ አባል ያልሆነች/ያልሆነ፤
የቅጥር ሁኔታ፡ በጊዜያዊነት
የስራ ቦታ አዲስ አበባ፣ማዕከላዊ ኢትዮጵያ፣ሶማሌ እና ቤኒሻጉል
አመልካቾች ከዚህ በታች በተቀመጠው የስራ ማመልከቻ ማስፈንጠሪያ በመንካት ማመልከት ይችላሉ፡፡

https://pw.nebe-elections.org/internship

ሴት አመልካቾች ይበረታታሉ።

ማሳሰቢያ፡-
ለሶማሌ ክልል ላይ አመልካቾች የክልሉን ቋንቋ ማወቅ ይጠበቅባቸዋል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
9.3K views07:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-03 10:51:14
ኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ6ኛው ዙር የጠቅላላ እና የድጋሚ ምርጫ ባልተካሄደባቸው የቤ/ጉሙዝ ፣ አፋር፣ ሶማሌ እና ማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች በሚገኙ 28 የምርጫ ክልሎች ላይ በጊዜ ሰሌዳው መሰረት የእጩዎች ምዝገባ ከሚያዝያ 21 እስከ ሚያዝያ 30 ቀን 2016 ዓ/ም ያከናውናል።

በዚሁ መሰረት ቦርዱ የተመዘገቡ ዕጩዎችን ዝርዝር በቦርዱ ድህረ ገጽ ላይ ለህዝብ በየጊዜው ይፋ ለማድረግ ባቀደው መሰረት ከሚያዝያ 21 እስከ ሚያዝያ 24 ቀን 2016 ዓ/ም በዕጩ ምዝገባ ማዕከል ቀርበው የተመዘገቡ እጩዎችን ዝርዝር ከታች ባለዉ ማስፈንጠሪያ ማየት ይችላሉ፡፡

የተወካዬች ምክር ቤት ዝርዝር

የክልል ምክር ቤት ዝርዝር
11.7K viewsedited  07:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-02 16:11:50
የሲዳማ ፌዴራሊስት ፓርቲን በተመለከተ ከቦርዱ የተሰጠ መግለጫ

የሲዳማ ፌዴራሊስት ፓርቲ ሊቀመንበር ከሀገር መውጣታቸውንና ፓርቲውንም የሚመራ ሰው መወከላቸውን ከውጭ ሀገር ሆነው ለቦርዱ ሲያሳውቁ ከፓርቲው አመራሮች መኃል ይህ በሊቀመንበሩ የተሰጠው የውክልና ሥልጣን ደንቡን የተፃረረ ነው የሚል ቅሬታ ለቦርዱ አቀረቡ፡፡ ቦርዱም ሊቀመንበሩ የሰጡት የውክልና ሥልጣን ከፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ አንፃር የተፈፀመ መሆን አለመሆኑን መረመረ፡፡ የፓርቲው መተዳደያ ደንብ አንቀጽ 22/1/ የፓርቲው ሊቀመንበር በማይኖሩበት ወቅት ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበሩ ሊቀመንበሩን ተክተው እንደሚሰሩ ደንግጓል፡፡ በዚሁ የፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ መሠረት ከሀገር በወጡት የፓርቲው ሊቀመንበር የተሰጠው ውክልና ደንቡን የተፃረረ በመሆኑ ቦርዱ ሳይቀበለው ቀርቷል፡፡ በመተዳደሪያ ደንቡ አንቀጽ 22/1/ መሠረትም እንዲፈፅም ወስኗል፡፡ ይሁንና በፓርቲው አመራሮች መኃል አለመግባባቱ እየጨመረ በመሄዱ በአዋጅ ቁጥር 1162/2011 አንቀጽ 74 (6) መሠረት ጉዳያቸው በባለሙያዎች ጉባኤ እንዲታይ ቦርዱ ወስኖ የባለሙያዎች ጉባኤ እያቋቋመ ይገኛል፡፡

ተጨማሪ ይመልከቱ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
ሚያዝያ 24 ቀን 2ዐ16 ዓ.ም.
11.2K viewsedited  13:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-05-02 11:06:24
የመራጮች ምዝገባ በኣፋር ክልል

Dooreenit Maysaqarra Qafar Rakaakayal
11.1K views08:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-29 13:59:29
11.0K views10:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ