Get Mystery Box with random crypto!

ዖዝያን.... በክብር ቢቀባ ፥በአስራ ሶስት አመቱ፤ በዙፋን ቢቀመጥ፥ ፀንቶለት ሹመቱ። እግዚአብሔር | መንፈሳዊ ግጥሞች ዘ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ

ዖዝያን....
በክብር ቢቀባ ፥በአስራ ሶስት አመቱ፤
በዙፋን ቢቀመጥ፥ ፀንቶለት ሹመቱ።
እግዚአብሔር ነገሩን፥ እየከወነለት፣
እልፍ እየማረከ፥ እልፍ ቢያስገዛለት።

በበረታ ጊዜ፥ ለጥፋት ታበየ፤
በመቅደሱ ሊያጥን፥ ጽና ይዞ ታየ።
ካህኑ የአሮን ልጅ፥ ዓዛርያስ ሳለ፤
ንግስናውን ትቶ፥ ንጉስ ልጠን አለ።

የእግዚአብሄር ፍርድ፥አይለወጥምና ፤
ተመለስ ንጉስ ሆይ፥ በዙፋንህ ጽና፤
ጽና ይዞ ማጠን፥ ያንተ አይደለምና፤
ቢለው አልሰማ አለ፥ ካህኑን ናቀና።

የትዕቢቱ መጠን፥ ዙፋኑን ነቀነቆ፤
ለየው ከንግስና፥ ካባውን አውልቆ።
ያደረገለትን ሀይል፥ ክብሩን ዘንግቶ፤
ንጉስ ልጠን አለ፥ ቤተመቅደስ ገብቶ።

እግዚአብሄር ቀሰፈው፣ ለምጽን አተመበት፤
በቤተ መንግስቱ፥ ልጁ ነገሰበት።
የማይነካ ነክቶ፥ንግስናው ተሻረ፤
ከአባቶቹ ርቆ፥ በእርሻ ተቀበረ።

ዛሬም ዖዝያን ሆይ!
በበረታህ ጊዜ፥ ጌታህን አትርሳ፤
እርሱ ነው የሚሰጥ፥ እርሱ ነው ሚነሳ።
ካህኑን አትንካ፥ የጌታን አገልጋይ፤
ቁልፍ አለና በእጁ፥ የመንግስተ ሰማይ።
++++
አንድ ቤተክርስቲያን
አንድ ሲኖዶስ
አንድ ፓትሪያርክ
አንድ መንበር
+++++
ሰማይ ስማ፥ ምድር አድምጪ፤
ቀን ወጣልኝ ብለሽ፥ ከሕጉ እንዳትወጪ።
በበደል ላይ በደል፥ እየጨመራችሁ፤
ዖዝያኖች ዛሬም፥ ትቀሰፋላችሁ።
++++++
ታዜና
      #መንፈሳዊ_ግጥሞች
      t.me/Menfesawigetmoch