Get Mystery Box with random crypto!

ጥያቄ ለክርስቲያን ወገኖች እንደሚታወቀው ትክክለኛው #አምላክ_ሁሉን_አዋቂ_ነው። የትኛውም አማ | 🍂 ረውደቱል ኢስላም የቁርአን እና የተርቢያ ማዕከል 🌿

ጥያቄ ለክርስቲያን ወገኖች

እንደሚታወቀው ትክክለኛው #አምላክ_ሁሉን_አዋቂ_ነው።

የትኛውም አማኝ በዚህ ሀሳብ 100% ይስማማል እናም ጥያቄዬን እንደሚከተለው አቀርባለሁ።

ኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ ከሆነ ታድያ ኢየሱስ በራሱ አንደበት ለምን እንዲህ አለ?

ኢየሱስ እንዲህ አለ:– ““ነገር ግን ስለዚያች ቀን ወይም ስለዚያችም ሰዓት #ከአብ #በቀር፣ የሰማይ መላእክትም ቢሆኑ፣ #ወልድም ( #ኢየሱስም ) ቢሆን፣ #ማንም_አያውቅም።”
[— የማርቆስ ወንጌል 13፥32]

ዮሐንስ ወንጌል 5:30 ኢየሱስ እንዲህ አለ:— "እኔ ከራሴ አንዳች ላደርግ አይቻለኝም፤ እንደ ሰማሁ እፈርዳለሁ ፍርዴም ቅን ነው፥ የላከኝን ፈቃድ እንጂ ፈቃዴን አልሻምና። ብሏል

ኢየሱስ ክርስቶስ በራሱ አንደበት እንዲህ አለ:–
" #አብ ( #እግዚአብሄር ) ሲያደርግ ያየውን ነው እንጂ #ወልድ ( #ኢየሱስ ) ከራሱ ሊያደርግ ምንም አይችልም።፤ (ዮሐንስ 5:19-20)

ኢየሱስ ክርስቶስ በሌላ ቦታ ላይ በራሱ አንደበት እንዲህ አለ:–
#ከራሴ _አንዳች_እንዳላደርግ በዚያን ጊዜ ታውቃላችሁ። (ዮሐንስ ወንጌል 8:28)

የሚገርመው ግን አምላክ የተባሉት ኢየሱስ ክርስቶስ ስለሚመጣው ነገር ወይም ስለወደፊቱ ምንም #አላውቅም ማለቱ ነው።

ማቲዮስ ወንጌል 24፥36
<<ስለዚያች ቀንና ስለዚያች ሰአት ግን ከአባት ብቻ በቀር የሰማይ መላእክትም ቢሆኑ ልጅም ቢሆን የሚያውቅ የለም>> ይላል።

እነዚህ 5 አንቀፆች ላይ ጥያቄዎች አሉን:–

#1ኛ ወልድ (ኢየሱስ) አምላክ ከሆነ እና ከአብ (ከእግዚዘብሄር) ጋር እኩል ስልጣን አለው ከተባለ እንዴት ወልድም (ኢየሱስም) አያውቅም አብ (እግዚአብሄር) ብቻ ነው ሚያውቀው ሊል ቻል ?

#2ኛ ብዙዎች ወልድ (ኢየሱስ) ያላወቀው እኮ #በስጋው_ነው ይሉናል።
ታዲያ #እውቀት_የስጋ_ባህሪ_ነውን ?

#3ኛ ወልድ (ኢየሱስ) በስጋው ከሆነ ያላወቀው መንፈስ ቅዱስስ በምኑ ነው ያላወቀው?
ምክንያቱም ቃሉ የሚለው #ከአብ_በቀር_ማንም_አያውቅም ስለሚል

ይህም ማለት በአጭሩ ወልድ(ኢየሱስ) እና መንፈስ ቅዱስ (ሰራፂ) በጭራሽ አያውቁም ነገር ግን አብ (እግዚአብሄር) ግን ብቻውን ያውቃል ማለት ነው።

#4ኛ አብ (እግዚአብሄር) ወልድ (ኢየሱስ) መንፈስ ቅዱስ (ሰራፂ) በስልጣን በመለኮት በአገዛዝ እኩል ናቸው የሚል ትምህርታቹን ውድቅ አያደርገውም ወይ?

ምክንያቱም አንዱ የሚያውቀውን ሌላው አያውቅምና ታድያ እንዴት #ስላሴ ((1+1+1= 1 ( አንድ ናቸው ማለት ይቻላልን ?)

መልስ በማስረጃ
https://t.me/LAILAHA_ILELLAH_ISLAMIC
https://t.me/LAILAHA_ILELLAH_ISLAMIC