Get Mystery Box with random crypto!

ንቂ ኢትዮጵያ

የቴሌግራም ቻናል አርማ killuminati2 — ንቂ ኢትዮጵያ
የቴሌግራም ቻናል አርማ killuminati2 — ንቂ ኢትዮጵያ
የሰርጥ አድራሻ: @killuminati2
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 1.00K
የሰርጥ መግለጫ

እዚ ገፅ ላይ የምናነሳቸዉ ነገሮች
፩ ስለ ኢሉሚናቲ
፪ ስለ 5G
፫ ኢትዮጵያ ላይ ስለሚደረጉ ሴራዎች
፬ ስለ GMO
፭ ስለ ግብረሰዶማዊነት
፮ ስለ ማይክሮ ቺፕ
1% CONTROL THE WORLD
4% ARE SELL OUT PUPPETS
90% ARE ASLEEP
5% KNOW AND ARE TRYING
TO WAKE UP THE 90%
THE 1% DONT WANT THE
5% WAKING UP THE 90%

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-05-09 11:28:19 ስለ NIKE ጫማ ማወቅ ያለብን

Nike በአለማችን ተወዳጅ የሆነው Brand ጫማ ስያሜውን ያገኘው ከጥንት የግሪክ አማልክት የ Pallas(Titan) እና የStyx ልጅ ከሆነችው Nike ነው ፡፡Styx መሬትንና የሲዖልን መግቢያ የሚከፍል ወንዝ ነው ብለው ግሪኮች ያምኑ ነበር፡፡
Nike የጥንታዊ ግሪኮች ጣዖት የነበረች ሲሆን የፍጥነት የጥንካሬና የድል አምላክ ብለው ያመልኳት ነበር፡፡መመለኳም አሁን ድረስ ቀጥሏል፡፡

Nike በ Zeus(የጥንት ግሪክ ዋና አምላክ) የፍጥነት የጥንካሬና የድል አምላክ ለዘላለም እንደሆነች ቃል ስለተገባላት አምላክነቷ አሁንም ድረስ ቀጥሎ በእሷ ስም የተሰየሙት ምርቶች የሚከተሉት ናቸው፡
1.Honda motor cycles የ Nike'ን ምልክት እንደ አርማ/logo ይጠቀማል፡፡
2.በአሜሪካ anti aircraft missile system የ nike'ን ምልክት ይጠቀማል፡፡
3.በዋነኛነት የ nike ጫማ አምራች የ nike'ን ምልክት ይጠቀማል፡፡

ስለዚህ አብዛኞቻችን የምንጠቀመው Nike ጫማ ሰይጣንን የሚወክል ስለሆነ ልንጠነቀቅ ይገባል፡፡በዙ ሰወች "ካላመለኩት ምን ችግር አለው" ይሉ ይሆናል ነገር ግን እኛ የእግዚአብሔር ተከታዮች እንጂ የሰይጣን አደለንም፡፡ ሰይጣን አምላኪዎቹ ኢሉሚናቲዎች ብዙ በጀት መድበው ይህንን ሁሉ የሚከውኑት የሚያመልኩትን ሰይጣን ከፍ ከፍ ለማረግና የዓለም ህዝብን በማወቅም ሆነ ባለማወቅ የሱ አቀንቃኝ ለማረግ ነው።

አሁን አሁን ላይ ለእኛ ለክርስቲያኖች ጊዜው ከባድና በፈተናዎች የተሞላ ነው::እያንዳንዷን እርምጃችን ቆም ብለን ማሰብ ይገባናል፡፡ምክንያቱም እኛ ግሎባላይዜሽን በሚባል በዘመናዊ ባርነት የታጠርን ሰወች አብዛኛው እንቅስቃሴያችን በእኛ ሳይሆን የሰይጣን ጭፍራ በሆኑ ሀገሮች የተወሰነ ስለሆነ ነው፡፡የሚሰጡንን ቀጥታ እንቀበላለን ለምን ብለን አንጠይቅም። የእነሱን እንቀበላለን የእኛን እንንቃለን የእነሱ የሆነው ሁሉ ይጥመናል፡፡ ነገር ግን ምን ያህል ስለምንከተላቸው ሰወች ፣ ስለ አለባበሳቸው ፣ ስለምንመገበው ምግብ ፣ ስለምንጠቀመው ቴክኖሎጂ እናውቃለን?

አሁንም ለመንቃትና ለማስተዋል ጊዜው አረፈደም!

#ፀረ_ኢሉሚናቲዝም
464 views08:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-05 09:27:52
የኢትዮጵያ ዋና ስር መሠረታዊ ችግር - አንቀጽ 39

ምዕራባውያኑ ስለ አንቀጽ 39 በፈረንጆቹ አቆጣጠር በ2014 ዓ.ም የሰጡት የሴራቸውን ማብራሪያ አድምጡት። ሀገሪቱን በብሔር ብሔረሰብ መብት ማስከበር ስም በህገመንግስቱ እንዲካተት የተደረገው በማር የተለወሰ መርዝ አንቀፅ አደገኝነት በሰፊው ተብራርቶበታልና አድምጡት ሼርም ተደረጋጉት። አዲሱ ትውልድ ሊነቃና ካለፈው ታሪኩ ሊማር ይገባዋልና።
424 views06:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-04 09:11:41 ንቂ ኢትዮጵያ pinned «ኦርቶዶክስን በኦርቶዶክሳውያን የማዳከም አዲስ ስልት! ባለፉት የታሪክ ገጽታዎቻችን ውስጥ በጉልበትና በይፋዊ ተቃርኖ ኦርቶዶክስን ከኢትዮጵያ ለማጥፋት ሲደረጉ የነበሩ እንቅስቃሴዎች ኹሉ አልተሳኩም፤ እንዲያውም የበለጠ ሲያጠናክሯትና ሲያስፋፏት ተስተዋሉ እንጂ፡፡ ለምሳሌ፡- በግራኝ አህመድ ወረራ ዘመን ኦርቶዶክሳውያኑን በግዳጅ የማስለም ድርጊቶች ተፈጽመው ነበር፤ ሕዝቡም ወደ እስልምና ሲገባ አምኖበት ሳይኾን…»
06:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-04 09:11:33 ኦርቶዶክስን በኦርቶዶክሳውያን የማዳከም አዲስ ስልት!

....የቀጠለ

(5) ከዚኽን በፊትም በተለመደው የፖለቲካ ሴራ አካሔድ መሠረት ቅዱስ ፓትርያርኩን ከመንበር አውርደው በሌላ ተረኛ ለመተካት ባለሥልጣናቱ ፊት ለፊት መምጣቱን አልፈለጉትም፡፡ እናም፥ መጀመሪያ ቅዱስነታቸውን እነርሱ ‹‹ጁንታ›› ከሚሉት አካል ጋር ፈርጀው ለማሸማቀቅ፣ በምእመኑ ዘንድ ለማስጠላትና ‹‹በፈቃዳቸው ለቀቁ›› ለማስባል ሞከሩ፡፡ ‹‹እኔም ኦርቶዶክሳዊ
ነኝ›› የሚሉ፣ በተግባር ግን ያልኾኑ ‹‹መምህራን›› እና አክቲቪስቶችን ከጀርባ ‹‹አይዟችሁ!›› እያሉ በጸያፍ አገላለጾች አስሰደቧቸው፤ ከልክ በላይም አፍ አስከፈቱባቸው፡፡ የቅዱስ ሲኖዶስን
ዋና ጸሐፊ ‹‹አይወክሉንም!›› የሚል መግለጫ አስሰጡ፡፡ ኦርቶዶክሳዊ ኹሉ ግን በሚገርም ኹኔታ እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ፣ እንደ አንድ ልብ መካሪ ኾኖ ‹‹ከአባታችን ጎን ነን!›› ብሎ አሳፈራቸው፡፡ ይኽንን የሕዝቡን ሥነ ልቡና ያስተዋሉት ፖለቲከኞቹ ከቅዱስነታቸው ጋር የ ግል ቅራኔ ያላቸውንና የሥልጣን ጥም ያሰከራቸውን ‹‹ጳጳሳት›› በኅቡዕ አደራጅተው መንቀሳቀስ ይዘዋል፡፡ ‹‹ደኅንነቶች ነን›› በሚሉ ሰዎችና ለተረኛው መንግሥት እንቀርባለን በሚሉ ‹‹አባቶች›› አማካይነት ‹‹መንግሥት የሚፈልገው ይኽንን ነው›› ብለው እያስወሩ በአባቶችን ውሳኔ ላይ ከወዲሁ ጫና ለማሳደር እየተሞከረ፣ ቤት ለቤትም ቅስቀሳዎች እየተደረጉ መኾኑ እየተሰማ
ነው፡፡ ገና ቅዱስ ሲኖዶሱ ሳይሰበሰብም፡- ‹‹ቅዱስ ፓትርያርኩ በሌሉበት ምልዓተ ጉባኤ እንደሚካሔድ፣ እንደራሴ እንደሚሾም›› ማስወራት ይዘዋል፡፡ የእኛን አባቶች እየተዋጓቸው ያሉት በእኛው አባቶች ነው የሚያስብለውም ይኸው ነው!

(6) ሕገ ቤተ ክርስቲያንን በማርቀቅና በማጽደቅ ሒደት ውስጥም የግለሰቦች ፍላጎትና የውጭ አካላት እጅ እየገባ እንደኾነ ተሰምቷል፡፡ ገና ሕጉ በቅዱስ ሲኖዶስ ታይቶ ሳይጸድቅ ‹‹የማስፈጸሚያ ሰነድ›› የሚል ረቂቅ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ውስጥ ባሉት የወቅቱ ፈላጭ
ቆራጮች አማካይነት ሌላ አጀንዳ ማስቀየርያ መዘጋጀቱም ታውቋል፡፡ ስሙን ‹‹ሕገ ቤተ ክርስቲያን›› እያሰኙት የቤተ ክርስቲያንን ጥቅም ለግለሰቦች ፍላጎት አሳልፎ የሚሰጠውን አካሔድ ግን ‹‹ሕጋዊ›› ለማስመሰል የሚሔዱበት ርቀት ያስተዛዝባል! ሌላው ቀርቶ ‹‹እኛ
መነኮሳት ነን፤ ንብረታችን ኹሉ የቤተ ክርስቲያን እንጂ የእኛ መኾን የለበትም›› የሚል ሐሳብ የሰጡ ሊቃነ ጳጳሳትን እንኳን ምን ያኽል ሲያገልሏቸው እንደነበር የምናስታውሰው ነው!

(7) የኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ሲኖዶሳዊ አንድነትና መዋቅራዊ ጥንካሬ ለጎሣ ፖለቲካቸው የመከፋፈል ሴራ አልመች ሲል የ16ኛውን መቶ ክፍለ ዘመን እሾኽ (‹‹ቅብዓት›› የሚባል ኑፋቄ)
በ21ኛው ክፍለ ዘመን መልሰው ለመትከል ምሥራቅ ጎጃምን የሚያስጨንቋትም አሉ፡፡
በየትኛውም የኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ታይቶና ተሰምቶ በማይታወቅ ሥርዓት ‹‹ጳጳሳት›› እንደተሾሙ ተነገረ፡፡ የቅዱስ ሲኖዶስን ምልዓተ ጉባኤ ትኩረት ለመሳብና አጀንዳውንም ለማስቀየርም ሲሉ ‹‹የጳጳሳቱ በዓለ ሢመት ተዘጋጅቷል›› ብለው የጥሪ ካርድ በተኑ፡፡ ይኽ ኹሉ ሲኾንና ከመደበኛው የቤተ ክርስቲያኒቱ መዋቅር ተደጋጋሚ አቤቱታ ለመንግሥት መዋቅሮች ሲቀርብ ግን ጆሮ ዳባ ልበስ ብለዋል፤ በአጥፊው ፋንታም ሰላማውያኑ ታስረዋል፡፡ ‹‹ተለያይቶ
የነበረውን ሲኖዶስ አንድ አደረግሁ›› ብለው የሚመጻደቁት አካላት ‹‹ሌላ ሲኖዶስ›› ለመፍጠር ለምን እንደሚሯሯጡ ግን ግልጽ አይደለም!
ኦርቶዶክስን በራሳቸው በኦርቶዶክሳውያን አማካይነት የማዳከም ስልት፤ አዲሱ የአጽራረ ቤተ ክርስቲያን ሴራ!

ከ ‹‹ግንጊልቻ›› መጽሐፍ፣ ምዕ.4፥ ገጽ.89-92 ላይ ባለው ሐሳብ መነሻነት የተጠናቀረ
434 views06:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-04 09:11:33 ኦርቶዶክስን በኦርቶዶክሳውያን የማዳከም አዲስ ስልት!

ባለፉት የታሪክ ገጽታዎቻችን ውስጥ በጉልበትና በይፋዊ ተቃርኖ ኦርቶዶክስን ከኢትዮጵያ ለማጥፋት ሲደረጉ የነበሩ እንቅስቃሴዎች ኹሉ አልተሳኩም፤ እንዲያውም የበለጠ ሲያጠናክሯትና ሲያስፋፏት ተስተዋሉ እንጂ፡፡ ለምሳሌ፡- በግራኝ አህመድ ወረራ ዘመን
ኦርቶዶክሳውያኑን በግዳጅ የማስለም ድርጊቶች ተፈጽመው ነበር፤ ሕዝቡም ወደ እስልምና ሲገባ አምኖበት ሳይኾን ተገዶ ስለነበር ጊዜ እስኪያልፍ በትዕግሥት ሲጠባበቅ ቆይቶ ነበር፡፡ እናም፥ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እነዚያ የመከራ ዘመናት ሲያልፉ ሃይማኖታቸውን እንዲክዱ
ተገደው የነበሩ ምእመኖቿን መልሳ ወደ ጉያዋ ለመሰብሰብ እንዲያስችላት ‹‹አንቀጸ አሚን›› የተባለ የማስተማሪያ መጽሐፍ አዘጋጅታ፣ ‹‹መጽሐፈ ቄዴር›› የተባለ የማጥመቅያ ሥርዓትም
ሠርታ ተልእኮዋን መልሳ ለማጠናከር ችላለች። ኦርቶዶክሳዊነትን ለማክሰም የተሠራ ሴራ ጭራሹን እንዲጠናከር ዕድል መፍጠሩን ይኽ አንዱ የታሪክ ምስክርነት ነው፡፡
በኋላ በጣልያን ወረራ ጊዜም ካቶሊኮች የእስልምናውን ክንፍ በመደገፍ ሁለቱ ‹‹የጠላቴ ጠላት ወዳጄ ነው›› በሚመስል መርሕ ተባብረው ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያንን ለማዳከም ሲሠሩ ነበር፡፡ ለምሳሌ፡- በካቶሊኮቹ ሴራ ‹‹ሁለቱ እሾሆች›› የተባሉ ቅባትና ጸጋ በኢትዮጵያ ምድር በተተከሉ ጊዜ ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን እነርሱን ለመንቀል ትግል ላይ ስትጠመድ እስልምናው ደግሞ ድምጹን አጥፍቶ ውስጥ ውስጡን ሲስፋፋ እንደነበር ተዘግቧል፡፡ በዚኽ ታሪካዊ ተሞክሮ መሠረት ደግሞ የጋራ ጠላትን እንዴት በትብብር መዋጋት እንደሚቻል ልምድ ተቀስሞበታል፤ ይበልጥ አዘምኖና አጠናክሮ መቀጠል እንደሚያስፈልግም የታመነበት ይመስላል፡፡
አሁንም በግላጭ ኦርቶዶክሳውያንን አስገድዶ ለመጠምዘዝ መሞከር የማይታሰብ ነውና ሌላ ስልት አስፈለጋቸው! ይልቁንም፥ ተፈጥሯዊ በኾነ መንገድ (biological strategy) ቤተ ክርስቲያኒቱ ራሷን በራሷ እንድታጠፋ ኹኔታዎችን ማመቻቸት አዲሱ ስልት ተደርጎ የተያዘ ይመስላል፡፡ ይኽ ስልት አንድ እንዲጠቃ የተፈለገው ተቋም ራሱን በራሱ እንዲያጠፋ መርዳት (helping the institution to self-suicide) የማድረጊያ ዘዴ ነው፡፡ ይኽ ተፈጥሯዊ
የመባሉም ምስጢር ችግሩን በሚመስል መፍትሔ የመከላከል ስልትን ስለሚከተል ነው፡፡
ለምሳሌ፡- በሥነ-ሕይወታዊ የጥናት ዘርፍ ትላትሎችን ከግብርና ሰብል ጥቃት ለመከላከል ሲፈለግ ለሰብሉ ጎጂ ያልኾኑ፣ ነገር ግን ትላትሎቹን የሚበሉ ሌሎች እንስሳት የማርባት ዘዴ
ማለት ነው፤ በዚኽ የተፈጥሮ ሚዛን (ecological balance) ይጠበቃል፡፡ ከሌሎች ስልቶች የበለጠም ውጤታማ ነው (ኬሚካልን የመሰሉ መፍትሔዎች ለጎጂ ተባዮች ተረጭተው
ጠቃሚዎቹንና ሰብሎችን ጭምር የሚያደርቁ ‹‹ጅምላ ጨራሽ›› ከመኾናቸውም በላይ ለአየር
ብክለት ስለሚያጋልጡ አይመከሩም)፡፡ ተባዮቹን የሚመስሉ ሌሎች ተጻራሪ ተባዮች ሲኾኑ ግን ተመሳሳይ የአኗኗር ዘይቤ ስላላቸው በቀጥታ ከመገናኘታቸውም በላይ ጎጂዎቹ ተባዮችን አዘናግተው (ዘመድ መስለው) እንዲያጠቁአቸው ዕድል ይሰጣቸዋል፡፡
ይኽንኑ ኹኔታ ወደ ተቋም ስናመጣው የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያንን ፊት ለፊት በመንግሥታዊ ሥልጣን ተጠቅመው፣ በሰይፍ አስፈራርተውና በሃይማኖታዊ ጉዳዮች ተከራክረው ማሸነፍ
እንደማይቻል ከታሪክ የተረዱት አካላት አንድነቷን ለመክፈል መጠቀም የጀመሩት አዲሱ ስልት መኾኑ ነው፡፡ ይኽ ስልት በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ላይ በቀጥታና በይፋ የሚሰነዝረውን ጥቃት በይፋ ሳያሳውቅ (ለትችት በማያጋልጠው፣ ነገር ግን የተሻለ ውጤታማ በሚያደርገው መልኩ) እንዲያዳክማት የሚያስችላቸው ነው፡፡
ይኽ ተፈጥሯዊ ስትራቴጂ ‹‹ራስን በራስ እንዲያጠፋ የመርዳት›› መርሕን ስለሚከተል ቤተ ክህነቱ እንደተጻራሪ ክንፍ በፈረጃቸው የእስልምናና ሌሎች የፕሮቴስታንት ቤተ እምነቶች ከመገዳደር ይልቅ በውስጡ ባሉት ሰዎቹ ተጠቅሞ፣ ስያሜውን በሚመስል ዘዴ፣ የራሱን ተልእኮ
የሚያፋጥንለት የሚመስለውን አሠራር መዘርጋት ይበልጥ ውጤታማ ያደርገዋል፡፡ መዋቅርን በመዋቅር፣ ጳጳስን በጳጳስ፣ ቤተ ክህነትን በቤተ ክህነት፣ ሲኖዶስን በሲኖዶስ፣ ማኅበራትን በማኅበራት፣ አሠራርን በአሠራር ተክቶ ከመጀመሪያው አቅጣጫዋ ወደ ሚፈለገው መሥመር ማስቀየስ፤ በሒደትም ግብዓተ መሬቷን ለመፈጸም እንደማለም ያለ ስልት ነው፡፡
ይኽ ከሰሞንኛ ኹኔታዎች አንጻር ምን ምን ነገሮችን እንድናስተውል ያደርገናል?

(1) ትናንት ‹‹የኦሮሚያ ቤተ ክህነት›› እያሉ ሲያጨናንቁን የነበሩ ‹‹ኦርቶዶክሳውያን›› ወንድሞቻችን ዘግይተው ደግሞ በመስቀል አደባባይ ጉዳይ፥ ‹‹ሙስሊም ወንድሞቻችን
ቢያፈጥሩበት ምን ችግር አለበት?›› እያሉ ሲከራከሩን አስተውለናል፡፡ የገዛ ወገኖቻችን ከተቀናቃኞቻችን ጎን ኾነው ሞገቱን፤ ኦርቶዶክሳውያንን በኦርቶዶክሳውያን መዋጋት ይሏል ይኽ
ነው!

(2) ይኽንኑ ጉዳይ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በጠቅላይ ቤተ ክህነቷ አማካይነት ተቃውሞ ስታቀርብ መንግሥት ደግሞ የእርሷኑ ሌላ መዋቅር (የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከትን) ተጠቅሞ
‹‹ይቅርታ›› አስጠየቀ፤ በመዋቅራችን አማካይነት መዋቅራችንን አጠቃው ማለት ነው!

(3) ለኦርቶዶክሳዊ ቀኖናት ደንታ የሌላቸውና ከመሰል እሴቶች ሊያንሸራትቱን የሚሹ ተሓድሶዎች ‹‹ኦርቶዶክሳውያን›› መስለው፣ ለትግራይ ሕዝብም እንደተቆረቆሩ አስመስለው
በበዓለ ሃምሳ ጾም ዐወጁ፡፡ ይኽንን ሲያደርጉ ግን ‹‹የገዳም አባቶችና የትግራይ ሊቃነ ጳጳሳት አዘዋል›› እያሉ ነው፡፡ ከእኛው ጾምና ትእዛዘ አበው ጋር ታክከው የእኛኑ ቀኖና ለመናድ የሚደረግ ሌላኛው እንቅስቃሴ!

(4) በውስጣችን ኾነው፣ ለሀገርና ለቤተ ክርስቲያንን አሁናዊ ጭንቀት መፍትሔ እንዳገኙ አስመስለው ‹‹ደጉ ንጉሥ ቴዎድሮስ ይገለጣል!›› የሚሉንም በዝተዋል፡፡ ለዚኽ ማሳመኛቸው
ደግሞ ‹‹ፍካረ ኢየሱስ›› እና ‹‹የገዳም አባቶች መልእክት›› የሚሉ የማግባቢያ አካሔዶችን ይጠቀማሉ፡፡ ገዳማውያኑ ግን በአንድነት ኾነው ‹‹መልእክቱ ከእኛ አይደለም!›› ማለታቸውን ልብ ይሏል፡፡

ይቀጥላል...
404 views06:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-27 01:30:07 ውሎ አዳር በጎንደር

(ታመነ መንግስቴ ነኝ)

ስሆነው ፣ሳደርገው የዋልኩትን በሰንበት ላውጋችሁ!

ይችን እሁድ የምትሰኝ ዕለት ፈጣሪ እኛን አበጅቶ እርፍ ብሎባታል ሲባል እሰማለሁ፣አንብቤማለሁ።

"ብታምኑም ባታምኑም ጦር ግንባር ሳለሁ ሁልጊዜ ጠዋት ጠዋት ለኢንጅነር ክፍሌ ሆሮ ደውየ የግድቡን ሁኔታ እጠይቅ ነበር" እንዳሉት የአገሬ መራሔ መንግስት(ሀሳብዎ ላይ ተሳስቸ ያላሉት ነገር ብየ ተሆነ እርስዎ ተሳስተው 'የኤርትራ ጦር አልገባም' እንዳሉት ይቁጠሩት) እኔም 'ብታምኑም ባታምኑም እሁድ የእረፍት ዕለት ናት' ብያችሗለሁ።

ግን ግን ጠቅላያችን "ነገርዮሹ ስራዎት መስሎኝ? ለምን ማሳመን አስፈለገዎት_እያ!?"

ደሞስ ኢትዮጵያ ውስጥ ምን የሚሉት አለማመን ነው? አሁን እኒህ የመኪናችን ዘዋሪ እስላሙ፣ጠዋት ቁርጥ ስንበላ'ቁርስ በልቻለሁ' ያሉን ኦርቶዶክሱ ጓዴ መኪና ውስጥ መተኛትን ተልባቸው መያዛቸውን ለማረጋገጥ 'ማርያምን?' ሲላቸው 'ማርያምን' ብለው የለም? ቢራስ አብረን አልጠጣንም? ይህችን እንቆቅልሽ አገር ምን ማድረግ ይሻላል? ማሳደግ

ውሎ አዳር በጎንደር፦

"ምን ተሰራ ፤ምን ተወራ
ጎንደር በጀግኖች ጎራ?
ይበሰራ፣
እውቀት ሐቅ ይነገራ።"

በሚል ዘፈን ተጀመረ።የመፃፍ ጸጋየን ተጠቅሜ "የጎንደር ወዳጆቸ ጋሽ ንዋይ"ጎንደር የወርቁ ልጅ ዘውዴ ናት እናቴ!" ያለላትን በሙሉ ስሟ ዘውዴ ወርቁ የምትሰኘን የጎንደር እናት ፈልጋችሁ አገናኙኝ " ብየ ለመንኩ።ልመናየን የሰማው እግዜር(እግዜር ግን ያነባል?) ቃልኪዳን(ቃልየ ብየ ስሟን አላቀልም) የዘውዴን ምትክ ፍቅርን አገናኙኝ።ፍቅር እኮ የባለከዘራው እህት ናት።እዚያ ቤት ያጎረሰችኝን ልጅ እግዜሩ መና ያውርድላት።እግዜሩ ግን ሳልሞትበት ለአፋር ሕዝብ የሚያጠግብ ውሃም ይስጠው።

ቀኑን ሙሉ ስንፈልገው የዋልነው ሰውየ ደመቀ ዘውዱ አይደለም? እኔስ ቤቱን፣ሚስቱን፣ልብሱን፣ጉርሱን አይቸ"እንደሰው ነው የምትኖር ጋሸ!?" ብየ ብደነቅበት "እህ እንደምን ልኑር?" አለኝ።

እኔማ እንደ 'ከንቲባ' አዳነች አበቤ ብየ ነበር።እናንተ 'እዳነች አበበች'የምትሉ ነገር ሰንጣቂዎች ግን ለአማራ ሕዝብ ምን አድርጋችሁለታል?

"አማራው ያጣው መሪ ነው።መሪዎች ለራሳቸው ክብር እንጅ ለሕዝቡ አይጨነቁም።"ብላችሁስ 'ማን አለህ'? ልትሉኝ አይደል?

'ደመቀ ዘውዱ' ልበላችሁና ዳግም አስከብቡት! እናንየ 'ጎንደር ባለ ማተብ ነው፤በደመቀ ዘውዴ እና ወልቃይት ጠገዴ አይደራደርም።'

የልቅ እንየ ታከለ የባህል አዳራሽ ብቅ ብለን እንመለስ። እዚያ 'ዶፔል ቢራ 22 ብር' ተብሎ ዋጋው በር ላይ የተፃፈለት ምን ያህል አስቀያሚ መጠጥ ቢሆን ነው? ጣፋጭ መጠጥና ልባም ጎንደሬ እማ 'ሽሽግ' ተደርገው እንደ መይሳው ካሳ ላለው የአገር ዋልታ ይሰጣሉ።የራስ አሊ እናት ተዋበችን ለዳግማዊ ቴዎድሮስ የዳሩለት እኮ ዋጋዋን ለጥፈው አይደለም!

'አንች በቀሚስ የምትዋቢው ጎንደሬ ወዳጀ እነበብሻለሁ!?"

"እኔን ጎንደር ጎንደር እኔን ጎንደር ያርገኝ
የበሉት ሲስማማ የፈለጉት ሲገኝ"

የባለከዘራው እህት ቤት የበላሁት እዚህ የማይፃፍ ነገር ተስማምቶኛል።እንደምሳ በልቸው እነሆ ራትም ሆኖኛል።ኤርምያስ አመልጋ ለምን በ24 ሰዓት አንዴ ብቻ እንደሚበላ ተገለጠልኝ ልበል እንዴ? ይልቅስ 'ከኤርምያስ አመልጋ ጋር ማዕከላዊ እስር ቤት ነበርኩ" ያለኝን መኩሪያ የሆነ ፋኖ_ሻለቃ ጠዋት ቃለ መጠይቅ አድርጌ አለሁ።

አዝማሪ አማረን...!

እንየ ታከለ ቤቷ ሞልቶባታል።ባልደረባየ"እናንተ ፈስሳችሁ ነው?" ያላቸው ጎንደሬዎች(ተሌላም አገር ሊመጡ ይችላሉ።አርብ ዕለት አዘዞ ጥይቱ እንደፈነዳ ዘብ(Police )ጣቢያ ተመቶ ሁለት ሰውም ሞቶ ገብተን ወላ ሐድያ ወላ ወላይታ ብቻ ሴቶች ለስደት ሊያመልጡ ሲሉ ተይዘው አላየንም እንዴ?) በሩን አልፈው መንገዱን እየዘጉት ነው።

ተስፋ ቆርጠን('ክርስቲያን ተስፋ አይቆርጥም'ሲባል እሰማለሁ።እስላምስ? እሱም አይቆርጥም።አብሮን የነበረው ሰውየ እስላም መሆኑን ተላይኛው አንቀጽ ጥፌ የለም እንዴ?) ስንጓዝ "ባላገሩ " የሚሉት የአዝማሪ ቤት አገኘን።

"እኔን ጎንደር ያርገኝ"

እዚያ ቤት ገብተን የገበየነውንስ ታልሞትኩ ተድሉ በሗላ አወጋችሗለሁ።ተሞትኩም አትደነቁ ሌላ ታመነ ወይም ሌላ እገሌ ያወጋችሗል።

"ከሰማይ በታች አዲስ ነገር የለም።" ጎንደርም በላሊበላ ዘመን ዝም ብላ ጋራ እና ሸንተረር ነበረች።ሗላ "እሽሩሩ ጎንደር"ተባለች።የፋሲል ግቢን አሃለች።አሁንም ደርግና ወያኔን ተቋቁማ እየቆዘመች፣እያስቆዘመችኝ አለች።

t.me/Gazetaw
655 views22:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-18 19:45:38
569 views16:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-18 19:45:30
515 views16:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-18 19:45:17 የብልፅግና ፓርቲና የብልፅግና ቤተክርስቲያን ምስል
የብልፅግና ቤተክርስቲያን ምስል ቢጫ፣ሰማያዊና ቀይ ሰዎች እጃቸውን ወደ ላይ ዘርግተው የሚዘሉ ሰዎች አናት ላይ መስቀል ከነ ፈነጠቀው ጸዳሉ ይስተዋላል፡፡ በአንፃሩ የብልፅግና ፓርቲና ሁለት እጆች ተዘርግተው ሰማያዊ፣ ቢጫና ቀይ ሰዎች በሰማየ ሰማያቱ ላይ የፈነጠቀውን የፀሐይ ብርሃን አይተው ሲጨፍሩ ይስተዋላል፡፡ የሁለቱም ቀለማቶች አንድ ዓይነት መሆናቸው ሰማያዊ፣ ቢጫና ቀይ ቀለማት መሆናቸውና ሦስት እጃቸውን ወደላይ አድርገው የሚዘሉ ሰዎች መሆናቸው ዝም ብሎ ገጠመኝ ሊሆን አይችልም እንላለን፡፡ የብልፅግና ቤተክርስቲያን የተጀመረው በአስራ ዘጠነኛው ክፍለዘመን የአዲስ ሃሳብ አፋላቂዎች ንቅናቄ ሲሆን በ1950 እኤአ በሃገረ አሜሪካ በመዳን ቅሪቶች ዘመን የብልፅግና ቤተክርስቲያን ነገረ መለኮት ተጀመረ፡፡ (www.Prosperity church logo)1 ድረ-ገፅ አይተው ትዝብትዎን ያጋሩ፡፡

የብልፅግና ፓርቲና ልዩ ልዩ የኃይማኖት እምነት ተቆማት
የብልጽግና መንፈሳዊ ትምህርት (ነገረ መለኮት) አስተምህሮት መሠረት ክርስቲያኖች ደህንነታቸው መጠበቅ አለበት ምክንያቱም መንፈሳዊና አካላዊ ህይወት የማይነጣጠሉና የማይለያዩ ተጨባጭና ነባራዊ ሁኔታ አላቸው፡፡ የምዕመናኖች ደህንነታቸው የሚተረጎመው አካላዊ ጤና እና በኢኮኖሚ ብልፅግና ይገለፃል፡፡ የብልጽግና ነገረ መለኮት መምህሮች አትኩሮቱን ለግለሰብ ሥልጣን መስጠት በመንፈሳዊና አካላዊ ጥምረት በጎ ጎን በመገንባት ያሳልፋል፡፡ ክርስቲያኖች በተፈጥሮ ላይ ሥልጣን ተሰጥቶቸዋል ምክንያቱም ክርስቲያኖች በእግዚአብሄር አምሳያ ስለተፈጠሩ ነው፡፡ በዚህም ምክንያት ክርስቲያኖች መንፈሳዊ ዓለማቸውን በማለማመድ በአካባቢያቸው የሚገኙ ቁስአካላዊ ነገሮች መጠቀም መቻል አለባቸው፡፡ የብልጽግና መንፈሳዊ ትምህርት መሪዎች ያለ አንዳች ፀፀት ኃጢአታችንን እንዲያስተሰርይልን፣ ከበሽታ ደዌን ለመፈወስ፣ ከድህነት አረንቆ ለመላቀቅ፣ ከመንፈሳዊ እርኩስነት ለመንፃት፣ ድህነትና በሽታ በህብረተሰቡ ዘንድ እንደእርግማን ስለሚቆጠር በእምነትና በእውነት ይህን የተሳሳተ አስተሳሰብ መስበር እንችላለን፡፡ ”Prosperity theology teaches that Christians are entitled to well-being and, because spiritual and physical realities are seen as one inseparable reality, interprets well-being as physical health and economic prosperity.[47] Teachers of the doctrine focus on personal empowerment,[48] promoting a positive view of the spirit and body. They maintain that Christians have been given power over creation because they are made in the image of God and teach that positive confession allows Christians to exercise dominion over their souls and material objects around them.[48] Leaders of the movement view the atonement as providing for the alleviation of sickness, poverty, and spiritual corruption;[49] poverty and illness are cast as curses which can be broken by faith and righteous actions.” 2

የዘመናዊ ሽብርተኛነት ታሪካዊ አጀማመር ከፈረንሳይ አብዬት ጋር ይያያዛል፡፡ በዘመኑ የሽብርተኛነት ሥር መሠረቱ መንስዔው ሥልጣኔ አሊያም የባህል ግጭቶች፣ ዓለም አቀፋዊ ትሥሥር፣ ኃይማኖታዊ ግጭቶች፣ የእስራኤልና የፓልስታይን ግጭት፣ አሊያም የራሽያ አፍጋኒስታን መውረር በሃገራት መህል የተከሰቱ ሽብርተኞነት ያካትታል፡፡ የዘመናዊ ሽብርተኛነት በግለሰብ ደረጃ በስብዓናችን ላይ የሚከሰት ብስጭት፣ የመገለል ስሜት፣ አሉታዊ የማንነት ጥያቄ፣ ራስን ማፍቀርና ማምለክ ንዴት እና ወይም የግብረገብነት ፈሪሃ እግዜብሄር ጋር ያለ ግንኙነት መላሸቅ ስሜቶች ይካተታሉ፡፡ በሃገራችን ኃይማኖታዊ ግጭቶች ወደ ዘርና ኃይማኖት ፍጅት (ጀጆኖሳይድ) ተሸጋግሮል፡
528 views16:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-18 19:43:10 https://images.app.goo.gl/4jJJ84b8S3Mn3Vv17
431 views16:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ