Get Mystery Box with random crypto!

ሽሽት ወይንስ በቀል በመغፊራ ቢንት ፉላን ክፍል አስራ9 | ኹሉድ ✍️

ሽሽት ወይንስ በቀል
በመغፊራ ቢንት ፉላን
ክፍል አስራ9
የመጨረሻው መጨረሻ

ሀይሚ የሰማችው ነገር ሁላ ህልም ሆነባት...... አሰበች ብዙ ነገር ተሸውዳለች፣ እሷ ብቻ ሳትሆን ጓደኛዋም ሀኒም፣ "ማሜ ይህንን ያደረገው ለበቀል ሆን ብሎ እንጂ በፍፁም ሀኒን አፍቅሯት አደለም" ስትል አሰበች። አምርራ ጠላችው...... ምን ማድረግ እንዳለባት ለሶስት ቀን ከቤቷ ሳትወጣ አሰበችበት ።
ከፖሊስ ሸሽቶ ወደሀዋሳ የሄደው ማሜ ሀዋሳ ከጓደኛው ጋ እየተፍታታ ነው። ሀይለኛ ጠጪ ሆኖል.... ፀፀት እንዲሰማው አይፈልግም..... ሀኒ፣ ሀይሚ፣ በሱ እጅ የተበላሹና ያለቀሱ ሴቶች መካሻ ህይወቱን ያበላሸችውን ሴት ገሏታል። "በቃ ተበቀልኩላቸው! ምን ላድርጋቸው ከዚ በላይ?" ይላል ይጠጣል ይጠጣል......... ሀኒን ሊያገኛት ፈልጎል። በዚ ደሞ ልትረዳው ምትችለው ሀይሚ ነበረች፣ እሱን ደሞ በስካር መንፈስ ሁሉን ነገር ድብልቅልቁን አውጥቶታል። ያለው ምርጫ ሳሚ ነበር....... ለሳሚ የተፈጠረውን ነገር ከመጀመርያ እስከ መጨረሻ ነገረው
"እኔ እስር ቤት ብገባ ና ሀኒ ብትመጣ ንገራት" ብሎ ነው የነገረው።
ሀይሚ ከሶስት ቀን ሀሳብ ቡሀላ ማሜን መበቀል እንዳለበት ወስና ስራዋን ለመስራት በለሊት ከቤት ወጣች። ቤተሰቦቿን ሀኒጋ ልሄድ ነው ብላ ነው የተናገረችው..... ትልቅ ጃኬት፣ ጥቁር ሱሪ፣ ትልቅ ቡትስ ጫማ፣ የወንድሟን ትልቅ ካፖርት፣ በሻንጣዋ ይዛለች። ጉዞ ወደ ሀዋሳ.........
ማሜን ፍለጋ ባደረገችው ፍለጋ መሰረት ያለበትን ቦታ ከነቤቱ አቤል ነግረዋታል። እሱን ለነሱ እንዳይነግራቸው "ሰርፕራይዝ ልታረጋቸው እንዳሰበች፣ ከማሜጋም ለመታረቅ እንዳሰበች፣ ሀኒንም ለማምጣት ማሜ አብሯት እንዲሄድ ስለፈለገች፣" እንደምትሄድ ስለነገረችው በደስታ ነበር ሁሉንም አድራሻ የነገራት። እዛ ከሄደች ቡሀላ አቤል በሰጣት መሰረት ሳሚን ና ማሜን ለሶስት ቀን ተከታተለቻቸው..................
ዛሬ ሀዋሳን ከረገጠች አራተኛ ቀኗ ነው። ስራዋን ልታጠናቅቅ ምሽቱን እየጠበቀች ነው። ከዛ በፊት ግን ለሀኒ አንድ ነገር ማድረግ አለብኝ ብላ ስላሰበች ለአህመድ ስልክ ደወለችለት፤ ድምፃን ሲሰማ አላመነም፣ ጠፍታበት ነበር፣ ልትነግረው ምትፈልገው ነገር ስላለ ከኡስማን ጋ እንዲያዳምጧት አስጠነቀቀችው።
"ምን አልባትም እኔን ከዚ ቡሀላ ላታገኙኝ ትችላላቹ! ስለዚ ስሙኝ" ብላ ጀምራ ስለተፈጠረው ነገር ሁላ ነገረቻቸው........ ዑስሚ በብስጭት "መሀመድ ያለበትን ንገሪኝ" አላት
"ስለሱ ነገ ነግርሀለው። አሁን ለሀኒ ፍጠኑላት" ብላ የደላላውን ስልክ፣ ያለችበትን ሚያቁ ሰዎችን ስልክ፣ ሁላ ሰጠቻቸው። እሷም ሁሉንም ነገር እየደወለች አጣርታ ቀኑን ሙሉ ሀኒን ሲያስሱ እና ሲያፈላልጉ ቆዩ። በመጨረሻም ተሳካላቸው። ሀኒን በስልክ አንድ አረብ ከአህመድ ጋ አገናኛት። ሀኒ አላመነችም ስልኩን ልትዘጋው ፈለገች፤ አህመድ እየደጋገመ "ይቅርታ" ይላታል "እባክሽ ይቅርታ ሀኒ ሁሉ ነገር በኔ ምክንያት ነው የተፈጠረው። የዛን ጊዜ ባልመጣ ይሄ ሁላ አይፈጠርም ነበር። እባክሽ ተመለሺ! እባክሽ!" እየለመናት ነው። ግን እንዴት ብላ ነው አይኑን ምታየው? እንዴት ብላ ነው በሌላ ወንድ የታቀፈው ገላዋን ለሱ ምትሰጠው? ከበዳት !ለመመለስ ፍቃደኛ አልሆነችም። ዑስማን ስልኩን ከአህመድ ተቀበለውና አናገራት ማትመጣ ከሆነ ለእናታቸው እንደሚነግራት፣ እሱም መሀመድ ካለበት ፈልጎ ገድሎ እስርቤት እንደሚገባ በእናቱ እየማለ ነገራት። ምትመጣ ከሆነ ሁሉም ነገር ይስተካከል። እናቷ ይህን ሲሰሙ ግፊታቸው ጨምሮ ሚሞቱ መሰላት..... ኡስሚ እስርቤት እድሜልክ ታስሮ ሲፈረድባት በምናቧ ታያት...... "እሺ መጣለው" አለችው ።

ቀኑ ለምሽቱ ቦታውን ለቋል..... በቃ የቀራት አንድ ነገር ነበር፣ ሀኒን መመለስ። ሀኒ ደሞ ደላላው ደውሎ ነገውኑ ወደ ኢትዮጵያ እንደሚልካት ቃል ገብቶላታል። ከዚ ቡሀላ ምንም አጠብቅም። ቤተሰቦቿም እሷን አይፈልጉም፣ ወንድሟ አለ። ከቤት ስትመጣ ይዛ የመጣችውን ልብስ ለበሰ፣ ከትልቁ ጫማ ውስጥ የደበቀችውን የአባቷን ሽጉጥ አወጣች። ወደ ማሜ ሄደች........ ከጭፈራ ቤቱ እስኪወጡ ጠበቀች....... ጭር ያለ ቦታ እስኪደርሱ ተከተለቻቸው.........ስክር ብሎ እየተንገዳገደ ነው። ሳሚ ከውሀላው ከአንዲት ሴት ጋ ይጃጃላል........ ፊትለፊቱ ሄዳ ቆመች አላወቃትም!
"ምን ፈለግሽ ደሞ አንቺ ዞርበይ ከዚ!" ፀጥ ብላው ቆመች ሊገፈትራት እጁን አነሳ፣ ወረወረችው በጣም ስለሰከረ ሄዶ ተዘረጋ። ያኔ ኮፍያዋን አወለቀችው ደነገጠ! በጭራሽ ሀይሚ ትሆናለች ብሎ አልገመተም! ሊሸሽ ፈልጎል! ምን ልታረግ እንደመጣች መጠርጠር ሳይጠበቅበት አውቋል። "ስሚ ሀይሚ" ሽጉጡን አወጣችው
"ማታውቂው ነገር አለ! ስሚኝ ተንተባተበ።
ደነፋች! እልህ ያዛት ሀኒላይ ያደረገው ነገር የእሷ ህይወት ፊቷ ላይ ድቅን አለባት። ግንባሩን አለችው....... አላቆመችም እየጮሀች ጥይቱን አርከፈከፈችበት...... ከዛ ወደጭንቅላቷ ወሰደችው........ ስራዋን ጨርሳለች መሞት አለባት ከጥይቱ በፊት ከውሀላዋ ጠንከር ያለ እጅ ቀደማት ፓሊስ! አንድ ያላስተዋለችው ነገር ይህንን ሁላ ስትፈፅም ከአጠገቧ ፓሊስ ካምፕ ነበር። ቦታውም ጭር ያለው እሷ አላወቀችም እንጂ የፓሊሶች ካምፕ በመሆኑ ማንም ሰው ደፍሮ አይጠጋም ነበር.............................

ጊዜው ነጎደ ሀይሚ ቤተሰቧቿ ባደረጉት ጥረት ወደ አ.አ ፓሊስ ጣቢያ ተሸጋግራለች። ዛሬ የመጨረሻው የፍርድ ቤት ቀጠሮ ሚሰጥበት ቀን ነው.........ሁሉም ቦታውን ይዞ ተቀምጧል........ ሀይሚ ያለምንም ክህደት ማሜን እንደገደለችው በራሷ መስክራለች፤ ዳኛው የቀኝና የግራውን ሰምቷ ክስ አንብቦ ጨርሷል...... ውሳኔውን ማሳለፍ ብቻ ነው የቀረው። ሁሉም በጉጉት ነው ሚጠብቀው......... ሀይሚ 25 አመት ተፈረደባት። የሰማችውን ማመን ያቃታት ሀኒ እሪታዋን ለቀቀችው። ሀኒ በድንጋጤ ዞር አለች...... ሀይሚ፣ አህሚ፣ ኡስሚ ችሎቱ ላይ ተገኝተዋል። ስላየቻቸው ደስ አላት። ሲወጡ ተገናኝተው ተቃቅፈው ተላቀሱ........ "ይቅርታ ሀይሚ" አለቻት "ሀኒ" የሚል ድምፅ አላቀቃቸው። ሳሚ ነው ሀኒን ሊያናግራት እንደሚፈልግ ለሁሉም ነገራቸው። ሀይሚ ወደእስር ቤት ስትሄድ እነሱ ሳሚን ተከተሉት..................
በሰሙት ነገር አዝነዋል....... ግን ምንም መፍጠር አይችሉም። ሁሉም ለማሜ አዝነዋል። ተበድሏል! መጥፎ በደል! ሀኒ ሳሚን ጠየቀችው "የት ተቀበረ?" ያደገበት ማዕከል ጓደኞቹ፣ ያሳደጉት ሞግዚቶች፣ ወደዚ መቶ እኛ እንቀብረዋለን። ስላሉ እዚ መቶ ነው የተቀበረው አላት። ቀብሩን ሊዘይሩ ተያይዘው ሄዱ.................

ከአምስት አመት ቡሀላ
ሀዩ የአክስቷን ቤት ለማሻሻጥ ከአሊጋ ወደ ኢትዬጲያ መታለች። ከአምስት አመት ቡሀላ የረገጠቻት ሀገሯ በጣም ናፍቃት ነበር............