2023-03-25 20:44:06
“እግዚአብሔርን #በመተማመን_የሚጠባበቁ ግን #ኃይላቸውን ያድሳሉ፤ እንደ #ንስር #በክንፍ_ይወጣሉ፤ #ይሮጣሉ፥ #አይታክቱም፤ #ይሄዳሉ፥ #አይደክሙም።”
(ኢሳይያስ 40፥31)
#Paster_Baye
ንስር የሚበርበት ሰማይ ሳይሆን: የሚበርበት ክንፍ ነበር ያጣው። ስለዚህ እራሱ #ያድሳል።
Restore ሳይሆን Renew ነው የሚያደርገው።
#Restore ማለት የነበረው መልሶ ለአገልግሎት ማብቃት ሲሆን #Renew ግን ቀድሞ የነበረው #አስወግዶ በሌላ #አዲስ መተካት ነው።
ንስር አሮጌው መንቁሩ: ጥፍሩ እንዲሁም ላባውን ሳይቀር አራግፎ ሌላ አዲስ ለብሶ ይነሳል።
አሁን ግን እንደ ቀድሞ ሳይሆን ቀድሞ ይበርበት ከነበረው ከፍታ በላይ ይበራል።
አንተም ጠላት ( ሰይጣን) ጣልኩት ካለው ስፍራ: በመንፈስ ቅዱስ አማካኝነት ተነስተህ: የቀድሞ ዝማሬህ: ጸሎት: አምልኮ እንደገና አንስተህ: ከዚህ ቀደም እንደነበረህ ሳይሆን በአዲስ ክብር ትገለጣለህ። አሁን #ትሮጣለህ: ደግሞም #አትታክትም: #ትሄዳለህ: #አትደክምም።
ስለዚህ ወዳጄ እንደ ንስር የምትበርበት ሰማይ ሳይሆን የምትበርበት ክንፍ በቅድሚያ ያስፈልግሃልና እግዚአብሔር በመተማመን ጠብቀው።
ምክንያቱም አውሮፕላን ከጎማው በላይ ክንፉ የተለቀው ከአንድ ሃገር ወደ ሌላ ሃገር የሚጓዘው በክንፉ ስለሆነ ነው: ጎማው የሚጠቅመው ለመቆም ነውና።
ያኔ ትናንት በረህበት በማታውቀው #Level ትበራለህ። እስከዛሬ አገልግለኸው: ሮጠኸው: በማታውቀው #ከፍታ ትሄዳለህ።
ተባርካችኋል ።
18 views17:44