Get Mystery Box with random crypto!

ጉብኝቴ አጠናቅቄ መጨረሻ አካባቢ አንድ ተቀፍሮ ለነገ የተዘጋጀ ብረት ብቻ የታሰረበት Footing | ✍ ልብ ወለድ በፅዮን ✍ fiction ❤️😘

ጉብኝቴ አጠናቅቄ መጨረሻ አካባቢ አንድ ተቀፍሮ ለነገ የተዘጋጀ ብረት ብቻ የታሰረበት Footing ጋር ደረስኩ…..ስመለከተው አሰራሩ የተወታተፈና ሴንተሩን ያልጠበቀ ሆኖ ታየኝ፡፡በርቀት ላይ ስራ ሲሰሩ የነበሩትን ጋሽ አህመድንና በሪሁንን ጠራዋቸው….ቦታውን በደንብ ለማየት ጨለም ስላለኝ እርግጠኛ መሆን አልቻልኩም…
‹‹ማነሽ እህት…ማን ነበር ስምሽ.እስኪ ባትሪው ይዘሺልኝ ነይ››
‹‹የትኛውን?›
‹‹አንዱን… ደህና የሚያበራውን››
‹‹እሺ›› ብላ ቆርቆሮ በቆርቆሮ ወደ ተሰራው እስቶር ሮጣ ሄደች...በፍጥነት በግራዋ አንድ ባትሪ በቀኞ ሌላ ባትሪ ይዛ መጣች፡
ሁለቱንም ተራ በተራ እየሞከረች ‹‹የትኛውን ልስጥህ ››አለቺኝ…..በዚህን ጊዜ በሪሁንና ጋሽ አህመድ መጥተው ስድስት ሜትር የሚረዝመው ጉድጓድ ውስጥ ገብተው ነበር…አይዳ ደግሞ ከልጅቷ ጎን ልክ እንደጋርድ ተገትራ ቆማለች፡፡እኔ የጉድጎዱ ከንፈር ላይ ቆሜ አንዱን ባትሪ ከልጅቷ ተቀበልኩና እታች ላሉት ለማቀበል ሞክር ጀመር… እሷም እንደእኔው የጉድጓዱ ከንፈር ጋር ቆማ ሁላችንም እንዲታየን ወደታች ማብራት ጀመረች፡፡
አያችሁ እዛ ጋር ያለው ኦቨርላፕ ትክክል አይመስለኝም..እስቲ ቼክ አድርጉት …››ላስረዳቸው ገና ስጀምር ….የቆምንበት አፈር የመንሸራተት ስሜት አሳየ.. እርስ በርስ ተያይተን ሌላ እርምጃ ለመውሰድ የሚያስችል የማሰቢያ ጊዜ ከማግኘታን በፊት ከእኛ ውጭ ያለ ከጥልቁ ሲኦል የተላከላ የሚመስል ኃይል ጎትቶ እንደጨመረን አይነት እግራችን ከዳንና ወደጉድጎዱ ተስፈንጥረን ገባን…
እንግዲህ የጉድጎዱ ጥልቀት ስድስት ሜትር ከሰላሳ ነው…. የሚቀበለን እንደአልጋ የተረበረበ ባለ 32 ዲያሜትር የአርማታ ብረት ንጣፍ እና ብረቱን ዙሪያውን አቅፎ የያዘው ወፍራም ፎርምወርክ (ጣውላ )ነው….ወይንም እድለኖች ከሆን ከታች ጉድጓድ ውስጥ ስራ ላይ በሚገኙትን ጋሽ አህመድ ና በሪሁን ጭንቅላት ላይ እናርፋለን…..እኛ ከከባድ ጉዳት እንተርፋለን…እነሱ ደግሞ ምን አልባት አንገታቸው ይቀነጠሳል፡፡
ስንት ሜትር ላይ እንደሆነ አናውቅም አዲሷን እስቶርን ኪፐር በአንድ እጄ በሌላ እጄ ደግሞ የአይዳን ቀሚስ ጨምድጄ ይዤ ነበር … ..በዛ ጭንቅ ላይ ሆኜ ‹‹አሁን እንዲሀ አንድ የተከበርኩ እና የተፈራው ፕሮጅት ኢንጂነር በሁለት ሴቶች መካከል ተጣብቄ ያየኝ ሰው ምን ይላል…?›› እያልኩ አስባለው ፡፡
…አዲሶ ልጅ . ኢየሱስ ድረስልኝ….ኢየሱስ ድረስልኘ.. እያለች ትጮኸለች
ከበታቻችን‹‹ አላዋክበር …አላዋክበር….››የሚል ድምፅ ይሰማኛል…….ጋሽ አህመድ መሰለኝ
.በጉጉት ወደሚሄድበት ሽርሽር ቦታ ለመድረስ እንደጎጎ ህፃን<<ቆይ አንደርስም እንዴ?..››ስትል ጠየቀች አይዳ ነች….ምንም የመለሰላት የለም
በእውነት ግን አንደርስም እንዴ ?ስል በውስጤ እራሴን ጠየቅኩ….ስድስት ሜትር ይሄን የህል እሩቅ ነው….?ነው ወይስ የቆሪጥ መንፈስ ወደ ጥልቁ የቢሾፍቱ ሀይቅ እየጎተተን ይሆን…?ምንድነው ጉዱ ?ቢሾፍቱ ሀይቅ አፋፍ ላይም የቤርሙዳ ትርያንግልን አይነት ታአምራዊ ማጅክ አለ እንዴ…?››በውስጤ ያሰብኩት ጭንቀት ወለድ ሀሳብ ነው፡፡
ከረጅምምምም የእድሜ ልክ ያህል ከሚረዝሙ ደቂቃዎች ቡኃላ መሬት ስናርፈ እኔ በሁለቱ ሴቶች መካከል እንደተጣበቅኩ ነበር.. እርስ በርስ ተያየን….
‹‹ወይኔ እማዬ ድረሽ…ቂጤ ተጨፈለቀ…››ለመጀመሪያ ጊዜ የሰማውት የአይዳ ንግግር ነው፡፡
‹‹ቂጥሽ መጨፍለቁ ምንም አይደል ነፍሽ ግን አለ?››
‹‹ቂጤ ከሌለ ነፍሴ ምን ያደርግልኛል?››የእሷ መልስ ነበር ፡፡
.ዙሪያችንን ስናይ እንደእስፖንጅ የሚያነጥር ቄጤማ የተነጠፈበት መሬት ላይ ነው ያረፍነው ….በሁለታችንም በእጃችን ያለው ባትሪ እየበራ ነው፡፡ያለንበት 2.5×2.5 ስፋት የተቆፈረ የfoothing ጉድጓድ ሳይሆን አንድ መለስተኛ ሳሎን ስፋት ያለው ግዙፍ ዋሻ መሳይ ክፍል ነው፡፡ ከእኛ ወደኣራት ሜትር እርቀት ላይ ጋሽ አህመድና በሪሁን ጎን ለጎን ተዘርረው እርስ በርስ በድንጋጤና በገረሜታ እየተያዩ ነው፡፡ምንድነው እየሆነ ያለው..?ለ foothing የተቀመጠው ብርት ከእኛ በአንድ ሜትር ርቀት ዘፍ ብሎ ቁጭ ብሎል፡፡ጣውላዎቹና መቀሰቻ እንጨቶቹ ተበታነው ወለሉን ሞልተውታል፡፡አይኔን ወደላይ አቀናው ትልቅ አለት ድንጋይ በመጣንበት አቅጣጫ ተቀርቅሮ አፈርና ብስባሽ ነገሮች ደፍነውታል፡፡አዎ ጉድጎዱ ተደርምሶል፡፡
በአስፈሪው የቢሾፍቱ ገደል ሀይቁ ጠርዝ ስር..ምን አልባትም ከሀይቁ ወላል በታችም ሊሆን ይችላል የአንድ ድርጅት ሰራተኞች የሆን ሁለት ሴት እና ሶስት ወንዶች በድምሩ አምስት ሰዎች የተፈጠሮ ታጋቾች ሆነናል…ከነነፍሳችን ተቀብረናል…ምን አልባትም አልቆልን ሊሆን ይችላል፡፡

ይቀጥላል .....


ሀሳብ አስተያየታችሁን
@Tsiyon_awit
አድርሱኝ

ቻናላችንን ይቀላቀሉ
@itsmetsiyearsemalj
@itsmetsiyearsemalj