የማብድ ቢመስለኝ ፣ ድንገት አንቺን ሳጣ አረቄ ቤት ሔጄ ፣ አረቄ ስጠጣ አንድ ግጥም ሰማሁ ፍቅርሽን ከልቤ ፣ ነቅሎ የሚያወጣ፡፡ ያውም መንገድ በሚል... ለመንገደኛ ሰው ፣ ሰካራም የፃፈው እዛ ጋ ቁጭ ብሎ... "ከዳችኝ" እያለ ፣ የሚለፈልፈው መንገድ የሚል ግጥሙ ፣ጆሮዬን ገረፈው፡፡ ጆሮዬ ሲገረፍ ፣ ጠባሳ ጣለብኝ ፣ ግጥሙን እንዳልረሳ "መንገድ አያደርስም መንገድ አይመልስም ፣ እግር ካልተነሳ!!!" እያለ ይገጥማል... ደጋግሞ ደጋግሞ ፣ ሌላ አይናገርም እሱም ልክ እንደኔ ... አንዷን በመሔዷ ፣ ሳያጣት አይቀርም፡፡ ብቻ ሰክሪያለሁ ለመንገደኛ ሴት ፣ የተፃፈ ግጥምን ፣ ጆሮዬ ያደሞጣል መሔድሽን ያየ እንደሌሌሽኝ ሲያውቅ ፣ ሊኖረኝ ይመጣል ይህ ነው መንገድ ማለት! የሰካራም ግጥምን ሰክሬ ስረዳው ማፍቀረ ሳይሆን ለኔ ፣ መርሳት ነው ሚጎዳው!!! ቻናላችንን ይቀላቀሉ ◦◦✧join .. @habtamu39 @habtamu39 @habtamu39 301 viewsⒽⓐⓑ ²¹ , 08:59