ሰሞንኛ ጨዋታ (በእውቀቱ ስዩም) . . . ትናንት ቀለል ያለ ራት ለመብላት ፈለግሁ ፤ እናም” ባጫ ህንጻ “ ውስጥ በሚገኘው የ” አማራ ባንክ” ቅርንጫፍ ጎራ ብየ በርከት ያሉ ሁለት መቶ ብሮችን ሸመጠጥሁ፤ ምግብ ቤት ገብቼ ፥ ምግቡ አላግባብ ውድ ከሆነብኝ ሂሳብ ለማካካስ ብዙ ነገሮች እጠቀማለሁ፤ ለምሳሌ ሬስት ሩም ገብቼ ለረጅም ጊዜ እቆያለሁ፤ ባጭሩ ፥ሬስት ሩምን ርስት ሩም አደርገዋለሁ፤ ያን ቀን ወደ ቤተ-ሰገራ ወሽንቤቱ ስራመድ መብራት ድርግምም አለ፤ ከግማሽ ሰአት የፈጀ ዘለግ ያለ ሽንት ሸንቸ ሳበቃ እያፍዋጨሁ ስወጣ የጽዳት ሰራተኛዋ ፥ “ "ሴቶች ሽንት ቤት ውስጥ መሽናትህ የሚያሳፍር ነው “ አለችኝ :: “ በዚህ ጨለማ ፥ ኪችን ውስጥ ባለመሽናቴ ልታደንቂኝ ይገባል “ ስላት ፈገግ አለችልኝ ፤ (ግን ጨለማ ከሆነ ፈገግታዋ እንዴት ሊታየኝ ይችላል ? ሰው ምን ይለኛል አይባልም? ) ባጭር ጊዜ የሌለ ተመቻቸን ፤መጨረሻ ላይ ቁጥርሽ ስንት ነው ?” ስላት፤ “ የጫማየ ወይስ የወገቤ” ብላ ስለመለሰችልኝ አጥብቆ ደበረኝ! ድብርቴን ለማባረር የሚከተሉትን ሁለት ቀደዳዎች አስታወስኩ፥ ጉዋደኛየ ባለፈው ለአለቃው ‘ የሞተር መኪና አደጋ ስለደረሰብኝ ዛሬ መምጣት አልችልም “ ብሎ ለአለቃው መልክት ሰደደለት፤ አለቅየው “ ይገርማል፤ ዛሬ በጀት መዝጊያ ስለተቃረበ በመስርያ ቤታችን ውስጥ ሰርፕራይዝ ፓርቲ አዘጋጅተን ነበር ፤ ለሰራተኞች ዳጎስ ያለ የገንዘብ ስጦታም አሰናድተናል፤ እንዲሁም ዳጎስ ዳጎስ ያለ መቀመጫ ያላቸው ሴቶች ፓርቲውን ያደምቁታል ፤ በዚህ ዝግጅት ተሳታፊ ባለመሆንህ የተሰማኝ ደስታ ማለቴ ሀዘን ወሰን የለውም ፤ ለማንኛውም ነፍስ ይማር፤ I mean እግዜር ይማርህ” ብሎ መለሰለት፤ ግብዣው በመጦፍ ላይ እያለ ረፍት የጠየቀው ጉዋደኛየ እንደቆሰለ አርበኛ በሁለት ወንድሞቹ ግራናቀኝ ተደግፎ ከች አለ፤ አለቅየው እንዳየው ምን አለ ? “ እያመመው መጣ! “ በዙ ጊዜ የሰይፉ ሾውን ስመለከት የራሴን ፈጠራ ነስነስ አደርግበታለሁ፤ ባለፈው ሰይፉ የሀይሌ ገብረስላሴን ፊት ይዞ የተፈጠረ ሰውየ አቀረበ፤ ሰውየው ሀይሌን እንዳገኘው “ ወንድሜ ! ብሎ እንደበረኛ ተጠመጠመበት ፥ ሀይሌ;- ወል እንግድ ! በአርባ ደቂቃ ውስጥ ለሚ ኩራ ደርሰህ ከተመለስህ ወንድሜ መሆንህን እቀበላለሁ” ሰውየው;- “ እሺ! አውቶቢስ ልያዝ ወይስ ራይድ ትጠሩልኛላችሁ? “ በመጨረሻ የዲኤን ኤ ምርመራ ተደርጎ ውጤቱ መጣ ; ሰውየው ;- በምርመራው መሰረት ወንድምህ መሆኔ ተረጋግጧል ፥ የሆነ ነገር አታካፍለኝም?” ሀይልሽ፤- ነገ ቢሮ ብቅ በልና የህይወት ልምዴን አካፍልሀለሁ” Share @fikireskemekabirtireka 173 viewsedited 17:41