Get Mystery Box with random crypto!

Extol ™

የቴሌግራም ቻናል አርማ extolimportandexport — Extol ™ E
የቴሌግራም ቻናል አርማ extolimportandexport — Extol ™
የሰርጥ አድራሻ: @extolimportandexport
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 342
የሰርጥ መግለጫ

EXTOL is an Import and Export firm with a vision of becoming an iconic commerce and service industry in Africa.

Ratings & Reviews

3.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-05-18 10:09:14
380 viewsAysheshim Tiruneh Alemu, 07:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-17 08:39:19
የስንዴ ዋጋ ንረት

ከሰሞኑን ሕንድ በሀገሯ የምግብ አቅርቦት እጥረት እንዳይከሰት በሚል የስንዴ ምርት ከሀገር እንዳይወጣ እገዳ ጥላለች።

ነገር ግን ይሄ እገዳ በሂደት ላይ የነበሩ የስንዴ ግብይቶችን አይመለከትም።

ሕንድ የስንዴ ምርት ወደ ውጭ እንዳይላክ ማገዷን ተከትሎ ከወዲሁ የስንዴ ዋጋ በአውሮፓ ሪከርድ በሆነ ሁኔታ ጭማሪ አሳይቷል።

የስንዴ ዋጋ ወደ 435 ዩሮ (453 ዶላር) በቶን ከፍ ማለቱ ተነግሯል። ባለፈው አርብ 422 ዩሮ ነበር።

የሰሞኑን የሕንድ ውሳኔ የተለያዩ ሀገራት የኮነኑት ሲሆን ውሳኔው በዓለም የስንዴ ገበያ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ይኖረዋል ብለዋል።

ሕንድ በስንዴ ሽያጭ ላይ እገዳ መጣሏ በተለይ በሩሲያ-ዩክሬን ጦርነት ምክንያት የስንዴ አቅርቦት የተቋረጠባቸው የአፍሪካ እና እስያ ሀገራት ሕንድን እንደ አማራጭ ለመጠቀም አስበው ነበር።

ሕንድ በዓለም ሁለተኛዋ ከፍተኛ የስንዴ አምራች ሀገር ናት።

ሩሲያ እና ዩክሬን ጦርነት ውስጥ ከገቡበት የካቲት ወር አንስቶ በተፈጠረው ስጋት ሳቢያ የዓለም የስንዴ ዋጋ 40 በመቶው ጨምሯል።

በዓለም የስንዴ ዋጋ መናር የማዳበሪያ እጥረትም እንደምክንያት ይነሳል።

@tikvahethiopia
114 viewsAysheshim Tiruneh Alemu, 05:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-15 17:02:29
ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች የማዕድን ሚኒስቴርን የሪፎርም ሥራዎች ተመለከቱ

ግንቦት 7/2014 (ዋልታ) የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት፣ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ እና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ የማዕድን ሚኒስቴርን የሪፎርም ሥራዎች ተመልክተዋል።

ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎቹና አመራሮቹ በሚኒስቴሩ የሚገኘውን የማዕድን ጋለሪ መመልከታቸውን የማዕድን ሚኒስትሩ ታከለ ኡማ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት አስታውቀዋል።

ሚኒስትሩ የሥራ ኃላፊዎቹ በተቋሙ ለነበራቸው ቆይታና ለሰጡት ገንቢ አስተያየት ምስጋና ማቅረባቸውንም ጠቁመዋል።

ለፈጣን መረጃዎች፦
ፌስቡክ https://bit.ly/3Ma7QTW
112 viewsAysheshim Tiruneh Alemu, 14:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-15 11:44:53 ለአበባ አምራቾች የመሬት አቅርቦት እንዲመቻች ተጠየቀ።


የኢትዮጵያ ሆርቲካልቸር አምራቾች እና ላኪዎች ማህበር ዳይሬክተር አቶ ቴዎድሮስ ዘውዴ ለኢትዮ የንግድ እና ኢንቨስትመንት መድረክ እንደተናገሩት በአሁኑ ሰአት በሀገሪቱ ያሉ የአበባ አምራቾች አጠቃላይ ይዞታ ከ1700 ሔክታር የማይበልጥ መሬት ነው፡፡


በዚህ መጠን ይዞታ ብቻ ሀገሪቱ ከ500 ሚሊዮን ዶላር በላይ ከአበባ ኤክስፖርት በየአመቱ እያገኘች መሆኑን ገልጸዋል፡፡

አቶ ቴዎድሮስ ይህ ተጨማሪ የመሬት አቅርቦት ቢኖር የሀገሪቱን የውጭ ምንዛሪ ገቢ ምን ያህል እንደሚያሳድገው አመላካች መሆኑን ተናግረዋል፡፡


በመሆኑም መንግስት ለአበባ አምራቾች ተጨማሪ የልማት መሬት እንዲያመቻች ዳይሬክተሩ ጠይቀዋል፡፡

የአበባ አምራች ዘርፍ በቀጥታ እና በተዘዋዋሪ በድምሩ 200 ሺህ ለሚጠጉ ዜጎች የስራ እድል ተፈጥሯል መባሉን ኢትዮ የንግድና ኢንቨስትመንት መድረክ ጽፏል፡፡

ግንቦት 07 ቀን 2014 ዓ.ም
106 viewsAysheshim Tiruneh Alemu, 08:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-14 13:15:48
ወደ ውጪ መላክ የነበረበት ከ235 ሺሕ ሜትሪክ ቶን በላይ እህል በክምችት መኖሩ ተረጋገጠ

ግንቦት 5/2014 (ዋልታ) ወደ ውጪ መላክ የነበረበት ከ235 ሺሕ ሜትሪክ ቶን በላይ የጥራጥሬ እና የቅባት እህል በክምችት መኖሩ መረጋገጡን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ገለጸ፡፡

ሚኒስቴሩ ከጠቅላይ ሚኒስቴር ጽ/ቤት ጋር በመተባበር በአራት ከተሞች በክምችት ተይዘው የሚገኙ የቅባትና ጥራጥሬ ሰብሎች በአይነትና በመጠን ለማጣራት ዳሰሳዊ ጥናት አካሂዷል።
በተደረገው የዳሰሳ ጥናትም፦

- በአዳማ ከተማ 6 ሺሕ 610 ነጥብ 18 ሜትሪክ ቶን የቅባት እህል እንዲሁም 55 ሺሕ 485 ነጥብ 75 ሜትሪክ ቶን የጥራጥሬ ሰብል

- በአቃቂ ቃሊቲ 3 ሺሕ 325 ነጥብ 95 ሜትሪክ ቶን የቅባት እህል እንዲሁም 2 ሺሕ 400 ነጥብ 22 የጥራጥሬ ሰብል

- በቡራዩ ከተማ 43 ሺሕ 569 ነጥብ 25 ሜትሪክ ቶን የቅባት እህል እንዲሁም 116 ሺሕ 844 ነጥብ 99 ሜትሪክቶን የጥራጥሬ እህል

- በገላን 57 ሺሕ 274 ነጥብ 13 ሜትሪክ ቶን የቅባት፣ 177 ሺሕ 514 ነጥብ 82 ሜትሪክ ቶን የጥራጥሬ እህል እንዲሁም 502 ነጥብ 06 ሜትሪክቶን ሌሎች ምርቶች በድምሩ 235 ሺሕ 291 ነጥብ 2 ቶን በክምችት መገኘቱ ተገልጿል።

በሚኒስቴሩ የግብርና ምርቶች መሠረተ ልማት ቡድን መሪ ታረቀኝ ሽበሺ ወደፊት የምርቶቹ ዋጋ ይጨምራል በማለት ምርትን በወቅቱ ወደ ውጪ ገበያ ከመላክ ይልቅ በክምችት ይዞ ማቆየት የሀገሪቱን ብሔራዊ ጥቅም የሚጎዳ መሆኑን መግለጻቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ አመላክቷል።
110 viewsAysheshim Tiruneh Alemu, 10:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ