Get Mystery Box with random crypto!

guzo wede jenet

የቴሌግራም ቻናል አርማ guzo5 — guzo wede jenet G
የቴሌግራም ቻናል አርማ guzo5 — guzo wede jenet
የሰርጥ አድራሻ: @guzo5
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 446
የሰርጥ መግለጫ

ጉዞ ወደ ጀነት አላማው
🌎 ዳእዋዉን ተደራሽ ለማድረግ ነው
የተለያዩ
የነቢያት ታሪክ
ሶሂህ ቡሀሪ ሀዲሶች
የሶሀቦች ታሪክ
ስለ ጤናዎ መረጃ
እዚህ ቻናል ላይ ያያችሁትን ማንኛውም ስተት እንድትነግሩን በአላህ ስም እንጠይቃለን
እንዲሁም ገንቢ ሀሳቦን ያጋሩን
ሁሌም ከጎናችን ላላችሁ ሁሉ አላህ ጀዛችሁን ይክፈላችሁ።
ለአስተያየትዎ @asiye9
@Asutii5

Ratings & Reviews

1.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

2


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2022-07-08 08:37:19 [ከዱዓዎች ሁሉ በላጩ የአረፋ ቀን ዱዓእ ነው፣ በዚህ እለት እኔም ሆነ ሌሎች ነብያት ከተናገሩት ሁሉ በላጩ ደግሞ"ላ ኢላሀ ኢለሏህ ወሕደሁ ላ ሸሪከ ለሁ፣ ለሁል ሙልኩ ወለሁል ሐምዱ ወሁወ ዓላ ኩሊ ሸይኢን ቀዲር"የሚለው ነው]
ይህንን በመደጋገም የአላህን ብቸኛ ተመላኪነት እንመስክር፣ተክቢራና ሌሎች ዚክሮችንም እናብዛ
http://t.me/guzo5
27 viewsedited  05:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-07 21:50:43 አረፋህ ሊመን አረፈህ!

ነገ ቤት የማፅጃ ወይ መጋረጃ የማውረጃ ቀን አይደለም። የኢድ ሸመታም ሆነ የመዝናኛ እንዲሁ!

ነገ አላህ የሰማይ ባለሟሎች ላይ በአረፋ ሰዎች የሚኩራራበት፤ የሰው ልጆች ከእሳት በገፍ ነፃ የሚባሉበት ከሁሉ በላይ ዱአዎች በሙሉ ተቀባይነት የሚያገኙበት እለት ነው።

ለይለቱል ቀድር ባትታወቅ የውሙ አረፋ ትታወቃለች። በለይለቱል ቀድር መላእክት ቢወርዱ በአረፋ አላህ (እሱን በሚመጥን አወራረድ) የሚወርድበት ነው!

ነገ አላህ በጊዜ ፀጋ ላጣቀማችሁ አንድ to do list ላካፍላችሁ

ጠዋት

ከፈጅር በፊት ከለይሉ ጥቂቱን መስገድ፣ ስሁር መመገብ እና ኢስቲግፋር ማብዛት!

ከሰላት በኋላ ቀጥታ ተክቢራ መጀመር ከዛም ፀሀይ እስክትወጣ ቁርአን፣ተህሊል፣ተህሚድ በአጠቃላይ በዚክር ማሳለፍ(አዝካረ ሰባህ ሳይረሳ)

ፀሀይ ስትወጣ የፀሃይ መውጣትን ሰላት እዛው ከመስገጃችን ሳንነሳ በመከወን ከረሱሉ (ሰ.ዐ.ወ) ጋር ሀጅ የማድረግን ምንዳ እንዲጎናጸፍ

ለቀን ኢባዳ ያግዘናል ብለን ካሰብን መጠነኛ እኝቅልፍ እንተኛ። ስንነሳ በትንሹ 4 ረክኣ ሰላተ ዱሃ እንስገድ!

ከሰአት

ከዝሁር ሰላት በኋላ ቁርዐናችንን እንቀራለን። የአረፋ ኹጥባ(ከመስጂደ ነሚራህ የሚተላለፈውን) መልእክት በጥብቅ መከታተል

ልባችንን ሊያረጥብ የሚችል መፅሐፍ ወይም ቪድዮ እየተመለከትን እራሳችንን እናርጥብ!

ከአስር በጥሎ እንዲሁ በቁርአን እና በዚክር መግሪብ 1 ሰአት አቅራቢያ እስኪቀረው ማሰለፍ!

የእለቱ ወሳኝ ሰአት ይህ ነው።

የተሰበረ የሚጠገንበት፤ የታመመ የሚፈወስበት፤ ተስፋ የቆረጠ ተስፋው ነፍስ ሚዘራበት ድንቅ ሰአት!

ዱኣ!!! ዱኣ ብቻ!

በዚህ ቀን ከእሳት ነፃ አለመባል ኪሳራ ነው። ምኞት ኖሮን ምኞታችንን ሳናሳካ መቅረት ቂልነት ነው!

ነገ አላህ አልመረጥንም እና እየተመለከታቸው ከሚኮፈስባቸው ጌታቸውን ለማላቅ በነጭ ተውበው ከአረህማን ድግስ ከሚታደሙት አልሆንም!

"አረፋ ተራራ ላይ መቆም ያልቻለ
አላህ ያሳወቀው ድንበር ላይ ይቁም

ሙዝደሊፋ ላይ ማደር ያልቻለ
በአላህ ትእዛዝ ላይ ይደር...ያቀርበዋልና!

ሚና ላይ እርዱን መከወን ያልቻለ
ምኞቱን ይረድ! ከፍ ይላልና።

ወደ ቤቱ በርቀት ምክንያት መድረስ ያልቻለ
ከደም ስሩ ቅርብ ወደ ሆነው የቤቱ ጌታ ይከጅል!" ኢብኑ ረጀብ

እርቅ ይበጀናል!

𝙝𝙪𝙯𝙚𝙮𝙛𝙖 𝙨𝙪𝙡𝙩𝙖𝙣
53 views18:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-07 11:08:24 #_የነብያያት_ታሪክ

#_ሙሳ_ዐለይሂ_ሰላም

እኔም ህዝቡ ለሁለት እንዳይከፈል ሰግቼ አንተ እስክትመጣ ድረስ ዝም አልኳቸው" አለው።ሙሳም ሀሩንን እዛው ትቶት ጥጃውን ወደቀረፀው ሰውዬ(ሳሚሪይ) ጋ በመሄድ፦"ምን አስበህ ነው እንዲህ ልትሰራ የቻልከው" አለው።
ሳሚሪይም፦"ያላዩትን ነገር (የጂብሪል
ባዝራ ፈረስ የረገጠችው መለምለሙን) አየሁ፤ከመልክተኛው
(ከፈረሱ ኮቴ) ዱካም ጭብጥ ዐፈርን ዘገንኩ፤(በቅርጹ ላይ)
ጣልኳትም፤እንደዚሁም ነፍሴ ሸለመችልኝ" አለው።
ጂብሪል ፊርዐውንን አሰቃይቶት ከባህሩ ውስጥ ሲወጣ የፈረሱ ኮቴ የረገጠችበትን አፈር ይህ ሰው ዘግኖ ይዞ ነበር። ከዚያም ሙሳ ጌታውን ሊገናኝ ሲሄድ ይህ ሳሚሪይ(ሳምራዊ) ከግብፅ የዘረፉትን ጌጣጌጥ አቀለጠ'ና የጥጃ ቅርፅ ሰረበት።
ከዚያም የጂብሪል ፈረስ ከረገጠችበት ቦታ የዘገነውን አፈር ደፋበት።ያን ግዜ ከወርቅ የሰራት የጥጃ ቅርፅ እንደ ጥጃ መጮህ ጀመረች። በመጨረሻም፦"ይህ እኮ ጌታችሁ ነው ሙሳ ረስቶት ሄዶ ነው" አላቸው'ና ኢስራኢላውያን ጥጃዋን ለ40 ቀናት ተገዟት። ሙሳም ለሳሚሪይ፦"ኺድ ላንተም በሕይወትህ
(ለአየኸው ሰው ሁሉ) መነካካት የለም ማለት አለህ፤ለአንተም
ፈጽሞ የማትጥሰው (አላህ የማይጥሰው የማይቀር) ቀጠሮ
አለህ፤ወደዚያም በርሱ ላይ ተገዢው ኾነህ ወደ ቆየህበት
አምላክህ ተመልከት" ብሎ ረገመው።
ኢስራኢላውያን በፈፀሙት ወንጀል የተነሳ በኪታቡ ተወርዶላቸው ከነበረውም አንድ ሰባተኛውን ከመፅሀፉ ተሰረዘ።
ኢስራኢላውያን ምንም ያህል ቢፀፀቱም አላህ ፀፀታቸውን መቀበል እንቢ በማለት ጥጃዋን ያመለኩትን ወገኖች እርስ በርስ እንዲገዳደሉ አዘዛቸው።በዚያ መሀልም የሞተው ሸሂድ እንደሚሆንም ነገራቸው።
ጥጃዋን በማምለካቸው የተፀፀቱትም ኢስራኢላውያን ለጥፋታቸው ማካካሻ እርስ በርስ መጨፋጨፍ ጀመሩ።በዚያ መሀልም በሽወች የሚቆጠሩ ኢስራኢላውያን ሞቱ። ይሄን ሲመለከቱም ሙሳ እና ሀሩን አላህን አጥብቀው መማፀን ጀመሩ።
አላህም ይቅርታውን አውርዶላቸው ግድያውን አስቆመላቸው።
ከዚያም ኢስራኢላውያን፦"ሙሳ የአላህን ድምፅ አሰማን" እያሉ ማስቸገር ሲጀምሩ ሙሳም ከኢስራኢላውያን የተወሰኑ እሙን ሰዎችን መርጦ እንዲፆሙ ካዘዛቸው በኋላ እዛ ጡር ተራራ ላይ ይዟቸው ወጣ።እነሱም፦"በል አሁኑኑ የአላህን ድምፅ አሰማን" አሉት።
ሙሳም እሽ ብሎ ወደ ተራራው ጫፍ ይዟቸው ወጣ'ና ልክ ተራራዋን ሲደርሱ የሆነ ዳመና ነገር መጣ እዚያ ዳመና ውስጥ ሙሳም ገብቶ ኑ አላቸው'ና አስገባቸው። በውስጡም ሲገቡ እርስ በርስ መተያየት እንኳን ተሳናቸው።
ዳመናውም ውስጥ እንደ ገቡ ሱጁድ አድርገው ሳለ ሙሳ እና አላህ ሲነጋገሩ ሰሙ።ሙሳም ከጌታው ጋር ያለውን ንግግር ከጨረሰ በኋላ ዳመናው ተገፈፈ። ያን ግዜ፦"በል ድምፁን ሰምተናል። እንድናምንህ ከፈለግክ እራሱን አሳየን" አሉት።
እንዲህ ሲሉ መቅሰፍት ወረደባቸው'ና ሁሉም በቅፅበት ሞቱ።
ሙሳም በጣም ተጨነቀ....እጁን ዘርግቶም፦"ጌታዬ ሆይ! ከህዝቤ መሀከል የተከበሩትን ነው መርጬ የመጣሁት፤ አሁን ሞቱ ብል ማንም እኔን አያምነኝም። ስለዚህ እባክህ አስነሳቸው" በማለት አላህን ሲማፀን ሰዎቹ ሩሆቻቸው ተመለሱላቸው።
ብድግ ብለውም፦" ሙሳ ሆይ! አንተ አላህን ጠይቀህ ምንም አይከለክልህም። ስለዚህ እባክህ እስቲ ሁላችንንም አላህ ነቢይ እንዲያደርገን ዱዓ አድርግልን" አሉት።
ሙሳም ዱዓ ሲያደርግ አብረውት የነበሩት ባጠቃላይ አንቢያእ ሆኑ።
ከዚያም ሙሳ ከጡር ተራራ ላይ ተውራትን(መፅሀፉን) ይዞ ወደ ኢስራኢላውያን በመመለስ ስለመፅሀፉ ማስተማር ሲጀምር፦"ይህ መፅሀፍ የሚለው ነገር ሁሉ ይከብዳል በዛ ላይ ሁሉንም ነገር ሀራም ይላል።አንቀበልህም" አሉት።
የኢስራኢላውያንን ጥመት አላህ ሲመለከት ጂብሪልን አዘዘው'ና በአቅራቢያቸው የሚገኘውን ትልቅ ተራራ ከስሩ ነቅሎ ወደ ሰማይ ከፍ በማድረግ ኢስራኢላውያን ላይ አንጠለጠለባቸው። ልክ ተራራው በላያቸው የሚወድቅ ይመስላል።
ከበስተኋላቸው ደሞ አስፈሪ የባህር ማዕበል መጣ።ከበስተፊታቸውም ደግሞ ነበልባል እሳት መጥቶ ድቅን አለባቸው።
ይህን ግዜ ሙሳ፦"የኢስራኢል ልጆች ሆይ! ይህ ያመጣሁላችሁን ተውራት(መፅሀፍ) የማትቀበሉ ከሆናችሁ ከላያችሁ በኩል ያለውን ተራራ አላህ ይጥልባችኋል፣ከበስተፊታችሁ ባለውም እሳት ያቃጥላችኋል፣ከበስተኋላችሁም ያለው ማዕበል ያጥለቀልቃችኋል" በማለት አስገደዳቸው።
እነሱም ይህን ጉድ ሲመለከቱ፤መሸሻም እንደሌላቸው በተረዱ ግዜ ለግዳቸው የተወረደላቸውን መፅሀፍ መርሀባ ብለው ተቀበሉ።
በዛን ጊዜ ኢስራኢላውያኑ መፅሀፉን ሲቀበሉ ሱጅድ አድርጉ ተብለው ሱጁድ ሲያደርጉ በግማሽ ግንባራቸው ተደፍተው በቆረጣ አይናቸውን እያንቀዋለሉ ተራራው እንዳወድቅባቸው ይጠባበቁ ነበር።በዚሁ አጋጣሚ የነሱ የሱጁድ ሱና በግማሽ ግንባር ሆኖ ቀረ።)
በዚህ ሁኔታ ላይ ሳሉ ከእለታት አንድ ቀን አንድ ልጅ የአጎቱን ንብረት ለመውረስ ፈልጎ አጎቱን ገድሎ ጣለው።ከዚያም ልጁ እራሱ ወደ ሙሳ በመሄድ፦"የአጎቴ ገዳይ ኤኬሌ ነው'ና ፍረደን" ብሎ ከሰሰ።ያ ገዳይ ተብሎ የተከሰሰውም እንዳልገደለው ተከራከረ።
ሙሳም አላህ እንዲፈርድ ተማፅኖት አላህም እስራኢላውያንን አንዲትን ላም እንዲያርዱ አዘዛቸው።
ሙሳ አላህ ያዘዛቸውን ለህዝባቸው ሲነግሩ ማላገጥ ጀመሩ፦"አንተ ሰው ሞቶብናል ፍረደን ብንልህ ላም እረዱ ብለህ ታሾፋለህ እንዴ!" በማለት።
ከዚያም በድርቅና፦"ምን አይነት ላም ናት" አሉ።
ሙሳም፦"እርሷ ያላረጀች ጥጃም ያልኾነች በዚህ መካከል ልከኛ የኾነች ጊደር ናት ብሏል አላህ" አላቸው።
እነሱም፦"ለኛ ጌታህን ጠይቅልን፤ መልኳ ምን እንደኾነ ለኛ ይግለጽልን" አሉት።
ሙሳም፦"እርሷ መልኳ ደማቅ ተመልካቾችን የምታስደስት ዳለቻ ላም ናት። ይላችኋል አላህ" አላቸው።
እነሱም፦"ለኛ ጌታህን ጠይቅልን፤ እርሷ ምን እንደኾነች ይግለጽልን፤ ከብቶች በኛ ላይ ተመሳሰሉብን፡፡ እኛም አላህ የሻ እንደኾነ በእርግጥ ተመሪዎች ነን" አሉ።
ሙሳም፦"እርሷ ያልተገራች ምድርን (በማረስ) የማታስነሳ እርሻንም የማታጠጣ (ከነውር) የተጠበቀች ልዩ ምልክት የሌለባት ናት። በማለት አላህ ይላችኋል" አላቸው።
ይህን ግዜ እንደዚህች አይነት ጊደር ፍለጋ ወጡ። ብዙ ካፈላለጉ በኋላ ይህችን ጊደር ራሷን አንድ በእናቱ መልካም የሚውል ልጅ ዘንድ አገኟት። ሊገዙት ሲሉ፦"አልሸጥም" አለ።
ብዙ ከተደራደሩ በኋለ በጊደሯ ቆዳ ሙሉ ወርቅ እንሰጥሀለን ብለው በዚህ ተስማምተው አረዷት።ካረዷትም በኋላ በጊደሯ ምላስ የሞተውን ሰውዬ እንዲመቱት ሙሳ አዘዛቸው።
ሬሳውን በጊደሯ ምላስ እንደመቱትም ሬሳው ተነስቶ፦"የወንድሜ ልጅ ውርስ ፈልጎ ነው የገደለኝ" ብሎ ተናግሮ ተመልሶ በድን ሆነ።
ከዚያም በሌላ ቀን ደግሞ ሙሳ ለኢስራኢላውያን ቆሞ ዳዕዋ እያደረገላቸው ሳለ፦"ሙሳ ሆይ! ከሰዎች ሁሉ አዋቂ ማን ነው" አሉት።
ሙሳም፦" እኔ ነኛ" ብሎ ሲመልስላቸው አላህም ሙሳን ወቀሰው'ና፦"ሙሳ ሆይ! ለኔ በሁለት ባህሮች መገናኛ ላይ አንድ ባሪያ አለኝ፤እሱም ካንተ በላይ አዋቂ ነው" አለው።
ሙሳም፦"ጌታዬ ያን ባሪያህን እንዴት ላገኘው እችላለሁ" አለው።

http://t.me/guzo5
863 views08:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-07 10:24:17 የዓረፋ ቀን ዱዓ
==========
የዐረፋ ቀን ከሚፈፀሙ ትላልቅና ወሳኝ ዒባዳዎች ውስጥ አንዱ ዱዓ ነው
||
የእዝነቱ ነብይ ነብዩ (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) በተከበረው ሐዲሳቸው እንዲህ ይላሉ፦
" خَيْرُ الدُّعَاءِ دُعَاءُ يَوْمِ عَرَفَةَ، وَخَيْرُ مَا قُلْتُ أَنَا وَالنَّبِيُّونَ مِنْ قَبْلِي : لَا إِلَهَ إِلَّا اللَّهُ وَحْدَهُ لَا شَرِيكَ لَهُ، لَهُ الْمُلْكُ وَلَهُ الْحَمْدُ وَهُوَ عَلَى كُلِّ شَيْءٍ قَدِيرٌ ".
*
"በላጭ ዱዓ ማለት የዐረፋ ቀን ዱዓ ነው። እኔንም ከእኔ በፊት የነበሩት ነብያቶችም ከተናገርነው ንግግር በላጩ ከአላህ በስተቀር በሐቅ የሚመለክ አምላክ የለም ብቻውን ነው ተጋሪም የለውም ንግስናም የእሱ ነው፣ ምስጋናም የእሱ ነው እሱም በሁሉም ነገር ላይ ቻይ ነው"። የሚለው ንግግር ነው።

http://t.me/guzo5
55 views07:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-06 06:30:15 ረሱል (ﷺ) ምርጡ ሞዴል!

ከአል‐አስወድ ቢን የዚድ رحمه ﷲ እንዲህ ይላል፦

﴿ما كانَ النبيُّ ﷺ يَصْنَعُ في بَيْتِهِ؟ قالَتْ: كانَ يَكونُ في مِهْنَةِ أهْلِهِ. فَإِذا حَضَرَتِ الصَّلاةُ خَرَجَ إلى الصَّلاةِ.﴾

“አዒሻን ነቢዩ (ﷺ) ቤት ሲሆኑ ምን ይሰራሉ? ብዬ ጠየኳት። እንዲህ አለችኝ፦ በቤት ውስጥ ሲሆን ቤተሰቦቻቸውን በስራ ያግዛሉ። የሰላት ወቅት በሚደርስ ሰዓት ለሰላት ይወጣሉ።”

ቡኻሪ ዘግበውታል: 5363

http://t.me/guzo5
69 views03:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-06 06:30:15 መልዕክት ለሚስቶች

➛ሚስት ሆይ ፀባይሽ ልክ እንደ አካልሽ ለስላሳ እንጂ ሸካራ መሆን የለበትም!!

➛ የትዳር መዝለቅ ዋናው ነገር ፀባይ ነውና ለባለቤትሽ ምርጥ ፀባይ ያለሽና ለስላሳ ሀኚለት!!

http://t.me/guzo5
61 views03:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-06 06:30:15 ካልወደድካት፣ ካላገባሃት ተዋት! ቀኗን አታኝከው! ውበቷ ሳይደበዝዝ ፤ የከጀለችውን አማርጣ በጊዜዋ ታግባ።

ጊዜ ለሴት ልጅ ከወንድ ልጅ በበለጠ ትርጉም አለው!

http://t.me/guzo5
61 views03:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-05 21:08:07
66 views18:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-05 07:32:02 #ባል የሌላት ሴት ምስኪን_ድሃ ናት አሉ።
ረሱል ሰለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም ለምን ተብለው ሲጠየቁ ?
"ሚስት የባሏን ፊት በፈገግታ ስትመለከት ቤተል ጧኢፍን
የተመለከተች ያክል ነው ደስታዋ አሉ።»

ሱበሃን አላህ
ለባሏ መልካም የሆነች ሴት
ለ ቤተሰቦቿ አርባ የሚሆን ለጀሃነም የተወሰኑ ካሉ በሷ ምክኒያት ነጃ ይወጣሉ አሉ።
ሱበሃን አላህ

#እህቴ #ሆይ
ለሷሊሁ መርሃባ በይ
አላህ ከሷሊሆች ያድርገን አሚን።

አንተም ወንድሜ ሷሊህ ሚስት ከፈለክ
ሳሊህ ባል ሆነህ ተገኝ
94 views04:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-04 05:06:16 #_የነብያት_ታሪክ

#_ሙሳ_ዐለይሂ_ሰላም

ኢስራኢላውያንም የግብፃዊያንን ብዙ መቃርብ ሲመለከቱ፦"ኧረ ሙሳ አንድ በለን እንጂ ደረሱብን፤ሊጨርሱን እኮ ነው" አሉት።
ሙሳም፦"አይ ጌታዬ ከኔ ጋር ነው። እራሱ ይመራኛል" አላቸው።
አላህም፦"ሙሳ ሆይ! በያዝከው በትር ባህሩን ምታው" ብሎ ወህይ አወረደለት።
ሙሳም በታዘዘው መልኩ ባህሩን ሲመታ ባህሩ ውስጥ አስራ ሁለት መንገዶች ተከፈቱ።ልክ ባህሩ እንደ ግድግዳ ቀጥ ብሎ ቆመ።
ኢስራኢላውያን ቁጥራቸው ምንም እንኳን ብዙ ቢሆንም ያ ሁሉ ህዝብ በአስራ ሁለት ጎሳዎች ብቻ የተወሰኑ ናቸው።ሁሉም ሰው ጎሳውን እየተከተለ በአስራ ሁለቱም በሮች ገብተው ባህሩን መሻገር ጀመሩ።
ኢስራኢላውያን ሁሉ ባህሩን መሻገር ጀምረው መሀል ላይ ደርሰው ሳለ ፊርዐውን ከነወታደሮቹ መጥቶ ከች አለ።ሲመጣ ማመን የማይችለውን ነገር ተመለከተ።
ፊርዐውን ባህር እንዲህ እንደግድግዳ ቆሞ ማየቱ ምንም እንኳን ቢያስደምመውም ስሜቱን ደበቅ አደረገ'ና ወደ ወታደሮቹ ዞር ብሎ፦"አታዩም እንዴ! ባህሩ ለኔ ክብር ተከፈተ።እኚህ ወራዳዎችን ገብተን እንያዛቸው ኑ" ብሎ ወታደሩን በሙሉ ይዞ ወደ ባህሩ ሊገባ ሲል ፈረሱ እንቢ አለው።
ቢለው፣ቢሰራው...ወዲያ ቢያዞረው ወዲህ ቢያዞረው ፈረሱ ምንም ሊታዘዝለት አልቻለም።ከዚያም ጂብሪል የምታምር ፈረስ ይዞ በወታደር ተመስሎ ወደ ባህሩ ዘልቆ ሲገባ የፊርዐውንም ፈረስ ጂብሪል የወጣባትን ፈረስ እያሸተተ ሲከተል ወታደሮችን የጫኑ ፈረሶችም በሙሉ ያችን ፈረስ ሲያይዋት ተከትለዋት ወደ ባህር ውስጥ መጋለብ ጀመሩ።
አላህም ሁሉም እስኪገቡ ዝም አለ።በመሀል ፊርዐውን ወደኋላ መመለስ ሲያስብ መንገዱን ሁሉ የፈረሶች ጋጋታ ሞልቶት ምንም መንገድ አጣ።ከዚያም ሁሉም ወታደር ባህሩ መሀል ሲገቡ ኢስራኢላውያን ደሞ ተሻግረው አለፋ።
አስቡት የአላህን ሂክማ...የመጀመሪያዎችን እያሻገረ መሀል ሲደርሱ ጠላቶችን ደሞ አስገባ፤ የመጀመሪያዎቹ ተሻግረው ሲያልቁ አላህ እንደግድግዳ ያቆመውን ባህር እዚያው ለቀቀውና አጥለቀለቃቸው።
ሀሉም በውሀው ተጥለቅልቀው ሲወራጩ ጂብሪል ፊርዐውንን ለየት አድርጎ ያዘውና በአፉ ጭቃ መሙላት ጀመረ።ለምን ጭቃ እንደሚሞላበት ታውቃላችሁ!!! ምናልባት አሳዛኝ ንግግር ተናግሮ እንዲህ ካመፀ በኋላ አላህ እንዳይምረው ነው።
በመጨረሻም ማዕበሉ እያንገላታው አንድ ወጣ አንዴ ገባ እያደረገው ሳለ፤ ድንገት አፉን እንደምንም ወጣ አድርጎ፦"አመንኩ፡፡ እነሆ ከዚያ የእስራኤል ልጆች በርሱ ከአመኑበት (አላህ) በስተቀር ሌላ አምላክ የለም፡፡ እኔም ከታዛዦቹ ነኝ" አለ።
ይህን ግዜ ሚካኢልም፦" ከአሁን በፊት በእርግጥ ያመጽክ ከአጥፊዎችም የነበርክ ስትሆን አሁን (አመንኩ ትላለህ)?" አለው።
አላህም፦"ዛሬማ ከኋላህ ላሉት(ትውልድ) ተዓምር ትሆን ዘንድ በድን ሆነህ (ከባሕሩ) እናወጣሃለን " አለው።
ይህ ሁሉ ሲሆን ይከታተሉ የነበሩት ኢስራኢላውያን፦"ፊርዐውን አልሰመጠም" በማለት ከነቢያቸው መከራከር ጀመሩ።ሙሳም ዱዓ አድርጎ የፊርዐውንን አስክሬን ከባህር ውስጥ አስወጥቶ አሳያቸው።
ከዚያም ሙሳ ሁለት ክፍለ ጦር አዘጋጀ'ና እያንዳንዱን ክፍለ ጦር በ 12000 (አስራ ሁለት ሺህ) ወታደሮች አደራጀ።
ሁለቱንም ክፍለ ጦሮች ወደ ግብፅ ሄደው በከተማው ያለውን እንዳለ ማርከው እንዲመጡ ላካቸው።ወታደሮቹም ብዙ ተጉዘው ግብፅን ለመዋጋት ሲገቡ ምንም ሚዋጋ አካል የለም። ሽማግሌዎች፣ህፃናት እና ሴቶች ብቻ ነበር የቀሩት ሁሉም የማዕበሉ ሰለባ ሆኗል።
ከዚያም ከተማዋ ላይ ያሉ ወርቆችን እና ጌጣጌጦችን ጠራርገው ተመለሱ።
እስራኢላውያን ትንሽ እንደቆዩም ሙሳን፦"የምንመራበትን አንድ መፅሀፍ ከጌታህ ዘንድ አምጣልን" አሉት።
ሙሳም አላህን ተማፀነው። አላህም ሙሳን ወደ ሰይናእ በመሄድ ጡር ተራራ ላይ እየፆመ ለ30 ቀናት እንዲያወድሰው አዘዘው።ሙሳም የእስራኢላውያንን ጉዳይ ለሀሩን አደራ ሰጥቶት ወደ ሰይናእ ሄደ።እዛም ሰላሳ ቀናትን እየፆመ ከሳለፈ በኋላ ድጋሚ 10 ቀናትን እንዲጨምር አላህ አዘዘው።
ሙሳም የጌታውን ትዕዛዝ በደስታ አጠናቀቀ።ከዚያም ሙሳ አላህ ኪታቡን ሊሰጠው ወደ ጠራው ቦታ እየተጓዘ ሳለ፤ ፆመኛ ስለሆነ አፉ እንዳይሸት ሰግቶ አንድ እንጨት በመስበር ቁጭ ብሎ ጥርሱን መፋቅ ጀመረ።
አላህም፦"ሙሳ ሆይ! የፆመኛ የአፉ ሽታ እኔ ዘንድ ከሚስክ ሽቶ በላጭ ውድ እንደሆነ አታውቅም እንዴ!!" አለው።
በዚህ ሁኔታ አላህ እና ሙሳ ብዙ ካወሩ በኋላ ሙሳ ይህን የሚያወራውን ጌታውን ማየት ፈለገ'ና፦"ያ አላህ እስቲ አንዴ ተገለፅልኝ'ና ልይህ" አለው።
አላህም፦"ሙሳ እኔን ማየት አትችልም ግን እስቲ ወደዚያ ተራራ ተመልከት እኔ ለተራራው እገለፅለታለሁ፤ ተራራው የኔን ኑር መቋቋም ከቻለ ላንተም እገለፅልሀለሁ። ግን ለማንኛውም ተራራውን ተመልከት" አለው።
የአላህም ኑር ትንሽ ለተራራው ሲገለፅ ተራራው መቅለጥ ጀመረ።ሙሳም የዚያን ተራራ መቅለጥ ሲመለከት እራሱን ስቶ መሬት ላይ ወደቀ።
ሙሳም ለተወሰኑ ሰዐታት እራሱን ከሳተ በኋላ ነቃ'ና፦" ጌታዬ ጥራት ይገባህ። ወዳንተ ተፀፅቻለሁ...እኔም ከሙእሚኖች የመጀመሪያው ነኝ" አለ።
አላህም፦"ሙሳ ሆይ! እኔ በመልክቶቼና በማናገሬ በሰዎች ላይ መረጥኩህ፡፡ የሰጠሁህንም ያዝ፡፡ ከአመስጋኞቹም ኹን።
በብርታትም ያዛት፡፡ ሕዝቦችህንም በመልካሟ እንዲይዙ እዘዛቸው፡፡ የአመጸኞቹን አገር በእርግጥ አሳያችኋለሁ።
እነዚያን ያለአግባብ በምድር ላይ የሚኮሩትን ከአንቀጾቼ በእርግጥ አዞራቸዋለሁ፡፡ ተዓምርንም ሁሉ ቢያዩ በርሷ አያምኑም፡፡ ቅንንም መንገድ ቢያዩ መንገድ አድርገው አይዙትም፡፡ ግን የጥመትን መንገድ ቢያዩ መንገድ አድርገው ይይዙታል፡፡ ይህ እነርሱ በአንቀጾቻችን ስለአስተባበሉና ከእርሷም ዘንጊዎች ስለኾኑ ነው።
እነዚያም በአንቀጾቻችንና መጨረሻይቱን ዓለም በመገናኘት ያስተባበሉት ሥራዎቻቸው ተበላሹ፡፡ ይሠሩበት የነበረውን እንጂ ይመነዳሉን" አለው።
ሙሳም ጌታው የሰጠውን ኪታብ ይዞ ወደ ህዝቡ መሄድ ጀመረ።ከምንም በላይ እሚገርመው ሙሳ የአላህ ኑር ያረፈበትን ተራራ ስላየ ብቻ ሙሳ እራሱ ማንፀባረቅ ጀምሯል ለዛ ተከናንቦ ነበር ሚሄደው።
ከዚያም ሙሳ ሀገር ሰላም ብሎ አላህ የሰጠውን ኪታብ ይዞ ሲከንፍ ወደ ህዝቡ ሲደርስ ያልጠበቀውን ነገር ተመለከተ።ህዝቡ የሆነ ጥጃ ነገር ቀርፀው ይህ አላህ ነው በማለት እያመለኩ ተመለከታቸው።
ሙሳም ቁጣው ድንበር አለፈ፤በእጁ የያዘውን ኪታብ በንዴት ወረወረው...ተንደርድሮ የወንድሙን ፂም እየጎተተ፦"ህዝቡ እንዲህ ያለ ጥመት ውስጥ ገብተው ሲጨማለቁ አንተ ምን እየሰራህ ነው?" አለው።
ሀሩንም፦"የእናቴ ልጅ ሆይ! መጀመርያ ፂሜን ልቀቅ። እኔ ዝም ልላቸው የቻልኩት መጀመርያ ተዉ ስላቸው ግማሹ ትቶ ግማሹ እንቢ አለ።......

ኢንሽዓሏህ
ይ.......ቀ.......ጥ.........ላ........ል፡፡

http://t.me/guzo5
1.0K views02:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ