Get Mystery Box with random crypto!

እውቀትን ፍለጋ

የቴሌግራም ቻናል አርማ ewiketinfilega — እውቀትን ፍለጋ
የቴሌግራም ቻናል አርማ ewiketinfilega — እውቀትን ፍለጋ
የሰርጥ አድራሻ: @ewiketinfilega
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 145
የሰርጥ መግለጫ

👍 join @EwiketinFilega
👍 አስተያየት ለመስጠት @Eshetu21bot
👉 join Facebook page :👇👇👇https://www.facebook.com/profile.php?id=100027751276659
👉 Twitter :👇👇👇👇👇 https://mobile.twitter.com/EshetuAyalewMo1

Ratings & Reviews

1.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-04-19 05:45:14 የመኖርን ጥበብ በእጅጉ የሚሻ አንድ ሰው ወደ አንድ ታላቅ ጠቢብ ዘንድ ይሄዳል። ግራ መጋባት የሚታይበት ይህ ሰው ጠቢቡ ጋር እንደ ደረሰ የጥያቄ መዕት ያወርድበታል። ጠቢቡም ሰው ሁሉንም ጥያቄ በጥሞና ከሰማ ቡአላ " የመኖርን ጥበብ አውቅ ዘንድ ካንተ ዘንድ መጣው። ቢቻልህስ ንገረኝ።" አለው።

ጠቢቡም ሰው እንዲ ሲል መለሰለት። "በ አንድ ወቅት ሰው ሁሉ የሚገረምበት አንድ ትልቅ ከመስታወት የተሰራ ትልቅ ቤት ነበር። ሁሉም ጥበብን የሚሻ የሚሄድበትና ጥበብን የሚማርበት። እናልህ ሁለት ሰዎች ይሄን ሰምተው ወደዛ ቤት ይሄዳሉ። ሁለቱም እጅግ የተለያዩ ናቸው። አንዱ ደስተኛ ተጫዋች ቅለል ያለ ህይወት የሚመራ ሲሆን ሁለተኛው በአንፃሩ ንዴታምና ብስጩ፥ ህይወትንም መክበድ የሌለባትን ያህል አክብዶ የሚያይ ነበር።

ወደ መስታወት ቤት ሲደርሱ ደስተኛው ሰው ቀድሞ ገባ። ወደ ቤቱም ሲገባ በጣም ተማረከበት። ፊታቸው እጅግ የበራ፥ ህይወትን በእጅጉ የሚያጣጥሙ አይላፍ ህዝብ ተመለከተ። ከበፊቱም በላይ እጅግ ተደስቶም ከመስታዎት ቤቱ ወጣ። ውጪ ቆሞ ላለው ለሌለኛው ሰውም ያየውን ነገረው።

እጅግ ብስጪ ንዴታሙ ሰውም ወደ መስታዎት ቤቱ ገባ። ያጋጠመውም ነገር ከበፊቱ እጅግ የተለየ ነበር። አእላፍ ደስታ የራቃቸውንም ሰዎች ተመለከተ። ቤቱን ከመውደድ ይልቅ ጥላቻ ሞላበት። እጅግ በተበሳጨ ቁጥር ቤቱ ውስጥ ያሉትም አእላፍ ሰዎች ብስጭታቸው ይጨምር ነበር። እሱ የሚያደርገው እያንዳንዱን ነገር እነርሱ በእጥፍ ይመልሱለት ነበር።" አለ ጠቢቡ ሰው።

ቀጥሎም "አየህ ሁለቱ ሰዎች ያዩት ነገር ሌላ ነገር ሳይሆን የራሳቸውን ምስል ነው። መስታወቱ የራሳቸውን ምስል መልሶ እያሳያቸው ነበር። እዚም ምድር ላይ የተለየ የመኖር ጥበብ የለም። አንተ የሆንከውን አከባቢህ ይሆንልሀል። ደስታን ከሰጠኸው እጥፍ አርጎ ይመልስልሃል። ፍቅር ከሰጠኸው አትርፍርፎ ላንተም ይሰጥሀል። ጥበቃ ካረክለት እርሱም መልሶ ይንከባከብሃል። ደግ ስትሆንለት ደግነት ታገኛለህ።

ላም ባልዋለበት ኩበት ለቀማ እንደሚባለው ሰው በ አሉታዊ ሀሳብ ተብትቦ ደግ ነገርን ከሰው ይጠብቃል። እየገደለ መኖርን ይፈልጋል። እያደማ መዳንን ይሽል። እየሱስ ይሄን ባንድ አርፍተ ነገር " የዘራኸውን ታጭዳለህ። " በማለት ገልፆታል። "ሊደረግልህ የምትፈልገውን አንተ ለሰው አድርግ ይላል።" ደግሞም እንዲህ ይባላል " አለም ላይ ማየት የምትፈልገውን ነገር አንተ ደግሞ እርሱን አርግ።"

አዎ ሰው ነገሮችን ሁለት ጎን እንዳላቸው ሳያቅ ይኖርና በመጨረሻም ይጎዳል። አሸናፊነትን እንጂ በሌላ ጎን ያለውን ሽንፈትን አይረዳውም። ህይወትና ሞት ፥ ደስታና ሀዘን ፤ መግደልና መሞት ፥ መውደድና ጥላቻ...... ወዘት የአንድ ነገር ሁለት ጎኖች ናቸው። አንዱን ብቻ ስንረዳ የእውነትን ግማሽ ተረዳን ማለት ነው። ሁለቱንም ስንረዳ ግን ሁሉም ይገባናል። ሀዘንን ለመሸሽ በሌሎች ሀዘንን አናመጣም። መውደድን ለማቆየት ሌሎችን አንጠላም።

ነገር ግን ተቃራኒ የሌለው አንድ ነገር አለ። እርሱም በ ፈጣሪ ተመስሏል። ይህ ተቃራኒ የሌለው አቻም ያልተገኘለት ነገር ፍቅር ነው። ፍቅር ጊዜን ጠብቆ የማይከዳ የተፈጥሮ ሀብት ነው። ገፅ በረከት ስጣታም ነው። ፍቅር ስንሰጥ ሁሉንም በሁሉ ውስጥ እናገኛለን።

ለዚህ የመኖር ጥበብ በጥቅሉ ያለ ቅድመ ሁኔታ ማፍቀር ነው። የሰው ልጅ ደጋግሞ ከመስማቱ ያልተገበረው ነገር ግን የሰለቸው ቃል። ሰው ተቃራኒ ያለውን ፍቅር ይዞ ይጎዳል። ፍቅር ይበለው እንጂ ይሄ በፍቅር ስም የሚነግድ ሌላ አይነት ስሜት ነው። ግዜን ጠብቆ ወደ ጥላቻ የሚሄድ ፍቅር ፍፁም ፍቅር አይባልም ። ፍፁሙን ፍቅር እሻ"!!!

@Ewiketinfilega
@Ewiketinfilega
280 viewsEshe Man, 02:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-07 18:48:22 ምክንያተ ተፈጥሮ

አንድ ሰው ወደ ቢራቢሮነት ሊፈለፈል የደረሰ የቢራቢሮ እንቁላል ከእነሽፋኑ ያገኛል፡፡ ከቀናቶቹ ባንዱ ቀን በእንቁላሉ ላይ አነስተኛ ቀዳዳ ያይና በትኩረት ይከታተለው ጀመር፡፡ ቢራቢሮዋ በተፈጠረው ክፍተት ለመውጣት ለሰዓታት ያህል ትግል ስታደርግ ቆየችና ያቃታት በሚመስል ሁኔታ ትገሏን ለተወሰነ ጊዜ አቆመች፡፡ ይሄን ሲመለከት የነበረው ሰውየ ቢራቢረዎን ሊያግዛት ወሰነና መቀስ በማምጣት የእንቁላሉን ሽፋን ቆረጠው፡፡ ቢራቢሮዋም በቀላሉ ወጣች፡፡ ነገር ግን ከተለመደው በተለየ ቢራቢሮዋ የተለነቆሰ ክንፍና ያበጠ ሰውነት ነበራት፡፡ ሰውየው የቢራቢሮዋን መብረር እየተጠባበቀ ነበር፡፡ ነገር ግን ምንም ለውጥ ሳያይባት ባለችበት ቆየች፡፡ ከቆይታ በኋላ መብረር እንደማትችል ተረዳው፡፡ በደግነት እርሷን ለማገዝ ያደረገው ነገር ከተፈጥሮ ህግ እንድትፋታ አድርጓት ነበር፡፡ ቢራቢሮዋ በትንሹ ቀዳዳ ለመውጣት የምታደርገው ጥረት በተፈጥሮ ህግ ልታልፍበት የሚገባ ጉዳይ ነበር፡፡

ተፈጥሮ ያስቀመጠችላት ህግ በትንሹ ቀዳዳ የራሷን ኃይል ተጠቅማ ታግላ በመውጣት እራሷን ብቁ ማድረግ ነበር፡፡ ምክንያቱም በምታደርገው የመውጣት ትግል በምክንያተ ተፈጥሮ ከሰውነቷ ውስጥ ያለውን ፈሳሽ በክንፎቿ አማካኝነት እንዲወጣ እና መብረር እንዲያስችላት የተዘረጋ የተፈጥሮ ስርዓት ስለሆነ፡፡ ይሄ ሂደት ግን ባለማወቅ ስለተቋረጠባት መብረር ሳትችል ሕይወቷም በዚሁ ተቋረጠ፡፡

ተፈጥሮ የእራሷ ህግ አላት፡፡ ህጎቿ ሁሉም ያለምክንያት አልተፈጠሩም፡፡ እንቁላል ከውጭ ሲሰበር ሕይወት ይቋረጣል ከውሰጥ ሲሰበር ግን ሕይወት ትቀጥላለች፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታ ቀጭኔም ልጇን እንደወለደች ግልገሏ ቁማ መራመድ እስክትጀምር ድረስ ደጋግማ በእርግጫ እንደምትመታት አንብቢያለሁ(ለደግነት መጨከን ይሉታል)፡፡ የጥላቻ ሳይሆን የፍቅር እርግጫ ምክንያቱም በተሎ ቁማ መሸሽ ካልቻለች ጠላቶቿ እንደሚያጠቋት የተፈጥሮ ህግ አስተምሯታልና፡፡

በአቋራጭ የማናልፋቸው ብዙ የተፈጥሮ ህጎች እንዳሉ ያስተምረናል፡፡ የሰዎችን አቅም ስናሳድግ እኛ እነሱን ተክተን እየሰራንላቸው ሳይሆን በእራሳቸው ታግላው እንዲችሉት፣ እንዲያውቁት ማድረግንም ያመላክታል፡፡ ቢራቢሮዋ በእራሷ ታግላ ብትወጣ ኑሮ ሕይወቷ መቀጠል ይችል ነበርና፡፡ አሁን ለሆንነው ሁሉ ያለፍንባቸው መሰናክሎች ወሳኝ ድርሻ አላቸው፡፡

ምንጭ፡ Inspiring story Butterfly


@Ewiketinfilega
@Ewiketinfilega
153 viewsEshe Man, 15:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-03 22:37:16 @ "እሴት ያለው ህይወት ኑር"

ተዘጋጀህም አልተዘጋጀህም ጉዳዩ አንድ ቀን ያበቃል።ከእንግዲህ የምትወጣ ፀሀይ አትኖርም። ደቂቃዎችም፤ ሰዓቶችም፤ቀኖችም የሉም።

እነዚያ የሰበሰብካቸው ነገሮች ሁሉ የወደድካቸውም ይሁኑ የረሳሀቸው ወደ ሌላ ሰው ይተላለፋሉ።ሀብትህ፣ዝናህ እና ዓለማዊ ሀያልነትህ መንምኖ እዚህ ግባ የማይባል ይሆናል።ምን ምን የግልህ እንደነበረ ወይም ምን ምን ዕዳ ሊከፈል ይገባ እንድነበረ ልዩነት አያመጣም።

ቂምህ ፣አትንኩኝ ባይነትህ፣ኩምታዎችህና ቅናትህ ጨርሰው ይጠፋሉ። እንደዚሁም ተስፋዎችህ፣ፅኑ ፍላጎቶችህ፣ዕቅዶችህ፣ የስራ ዝርዝሮችህ ጊዜ ያለፈባቸው ይሆናሉ።በፊት በጣም አንገብጋቢ ይመስሉህ የነበሩት ድሎችና ሽንፈቶችም በንነው ይጠፋሉ።ከየት መጣህ? ደስተኛ ወይስ መከረኛ ኑሮ አሳለፍክ፤በመጨረሻ ልዩነት አይኖረውም።መልከ ቀና ነበርክ ወይስ ጥበበኛ ልዩነት አያመጣም። ፆታህና የቆዳህ ቀለም ሳይቀር እዚህ ግባ የማይባል ኢምንት ጉዳይ ሆኖ ይቀራል።

እንግዲያው (ላንተ) ልዩነት የሚያመጣው ምንድን ነው? የኖርካቸው ቀናት፣ የእሴታቸው ልክ እንደምን ሊመዘን ይችላል?ለወደፊት ዋጋ የሚኖረው ስኬታማ ውጤት ሳይሆን በሰዎች ልቦና የሚጠራቀምልህ እሴትህ ነው። ልዩነት የሚያመጣው ምን ምን እንደገዛህ አይደለም ለሰዎች ምን ምን እንዳበረከትክ ነው እንጂ
በመጨረሻ ልዩነት የሚያመጣው ችሎታህ ሳይሆን ጠባይህ ነው።

ስንቶች መሰናበትህን እንዳወቁ ሳይሆን ፣ ለስንቶች አንተን
ያለማግኘት የሁልጊዜ እጦት እንደሚሆንባቸው ነው፡፡ የሚወዱህ
ሰዎች ውስጥ የሚቀረው ለምን ያህል ጊዜ እንደሚያስታውሱህአይደለም ፤ትውስታዎችህም አይደሉም ፤ እነማንን ለምን እንደምትታወሳቸው እንጂ::

እሴት ያለው ሕይወት መኖር ባጋጣሚ አይመጣም ፡፡ሁኔታዎች
የሚወስኑት ጉዳይ ሳይሆን፣ አንተ ራስህ መርጠህ የምትፈፅመው
ነው፡፡››


@Ewiketinfilega
@Ewiketinfilega
232 viewsEshe Man, 19:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-31 07:25:18 የአሁኗ ቅፅበት የመጨረሻ የሕይወት ጊዜህ ልትሆን እንደምትችል ማሰብ አያስፈራም?

ሁሌም ሌላ ዕድል ሲሰጥህ ይህንን በአእምሮህ ውስጥ አስገባ፣ ሁሉም ነገር እንደገና ላይመጣ ይችላልና ፣ምክንያቱም ሕይወት ሁልጊዜ ሁለተኛ ዕድል አትሰጥም ፣ በየጊዜው የሚመጡትን ዕድሎች እንደ ቀላል አድርገህ መውሰድ የለብህም።

አሁን የሚታየውን ነገር ሁሉ ለመጨረሻ ጊዜ እያየህ እንደሆነ በማሰብ ከልብ ነገሮችን ተመልከት ፣ ሁል ጊዜ እያንዳንዱን ደቂቃ በማስተዋል እንዲቆጥር ማድረግ አስፈላጊ ነው ፡፡
ሕይወት አጭር ናትና

አንድ ቀን ደስታ ቤቴ ይገባል ብለህ ደስታህን አትግፋ፣ ዛሬ ደስተኛ የምትሆንበት አንድ ነገር ይኖራል። የአሁኑን ደቂቃ በጥልቀት መመልከት ከቻልክ ሁል ጊዜም የሚያስደስት ነገር አታጣም ፡፡

ደስታ የችግሮች መቅረት አይደለም ፣ ግን በችግሮች መካከልም እንኳን የምስጋና መኖር ነው ፡፡ሁልጊዜ ደስተኛ ለመሆን ሊኖርህ የሚገባው አመለካከት ይህ ነው፣ አሁን ባለህ ነገር ደስተኛ ሁን ፣ቅፅበትህ የምታመጣውን የተትረፈረፈ ደስታ አጣጥም፡፡

ባለህበት ደስተኛ ካልሆንክ ወደ ምትሄድበት ስትደርስም ደስተኛ አትሆንም ፡፡ሕይወት አጭር ናት ፣ ለዘላለም አትኖርም ፣ ስለዚህ አሁን ደስተኛ ሁን ፡፡


@Ewiketinfilega
@Ewiketinfilega
@Ewiketinfilega
147 viewsEshe Man, 04:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-22 19:03:44 ወዳጄ ሆይ ባለሀብት ብዙ ያለው ሳይሆን ካለው ብዙ የሚሰጥ ነው።ከሚደልሉ አንደበቶች የሚመፀውቱ እጆች እጅግ ይልቃሉ ። ልግስና ማለት የኪሳችንን ቦርሳ መክፈት መቻላችን ብቻ ሳይሆን ልባችን መክፈት መቻላችን ነው።

ወዳጄ ሆይ የእውነት መሰረት ፍቅር ነው ።የፍቅር የመጀመርያ ምልክትና ርምጃ ልግስና ነው !የልግስና ጓደኛ ፍትሕ ነው ። የፍትሕ ፍሬ ደግሞ ስላም እና ሰዎችን መታደግ ነው ። ለሰዎች እርዳታን መሰጠት በእነሱ ውስጥ ፈጣሪን ማየት እና ማግኘት ነው።

ወዳጄ ሆይ ሰዎች በሚሰፈልጋቸው ግዜ እርዳ እነሱም በሚስፈልግህ ግዜ ይረዱሀል።ምንም ዓይነት የሕይወት ደረጃ ይኑርው፣
ከትኛውም እምነት ፣ ቀለም እና ዘር ይሁን፣
መልካምም ይሁን ክፉ ሁሉም ሰው በፈጣሪ የተፈጠረ መሆኑን አሰታውስ።

ወዳጄ ሆይ ለመልካም ስራ እጅን ለግስ "ልግስና የነፍስ ምግብ ነውና
ደስታ ለሚሰጥ አብዝቶ ይመለስለታል።
ጥሩ እርካታ ያገኘ ጥሩ ክፍያ እንዳገኘ ነው ።ባለንና በምናገኘው ነገር ኑሯችንን ስንመሰረት በምንሰጠው ነገር ደግሞ ሕይወታችንን እንመሰርታለን።

ወዳጄ ሆይ ለራስህ የምትፈልጋቸውን ሁሉ ለሁሉም ስጥ በትክክለኛው ስሌት ደስታን በሰጠኽው መጠን ትቀበለዋለህ።ደስታ በሰጠህ ግዜ እጥፍ ይጨመርልሀል።ሌሎችን መረዳት የመጀመርያው ንቃት እና ዕውቀት ነው፣ መንፈሳችንንም ወደ ላይ ክፍ ከፍ ያደርገዋል።

መልካም ስራን ለመስራት የምንሰዋው ኃይል ለጊዜው ዋጋ ቢስከፍለንም በመጨረሻ ግን በውስጣችን የሚሰጠን የደስታ መጠን ግን እጅግ የላቀ እና የበዛ ነው! ! ! ታላቅ የሆነ ጥበብ እና ማስተዋልንም ይዞ ይመጣል ።

ወዳጄ ሆይ ደስተኛ የመሆን ቀላሉ መንገድ መልካም ነገር ማድረግ ነው ።ውብ ነገርን ተመርኩዘው የሰሩት ስራ ሁሌም ውብ ነውና።

ኢትዮጵያ ሰላምሽ ይብዛ

@Ewiketinfilega
@Ewiketinfilega
157 viewsEshe Man, 16:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-19 08:33:28 ችግር!

የእምቅ
ብቃትህ ብቸኛ መውጫው ቀዳዳ!

“ያልገደለኝ ነገር ሁሉ ያጠነክረኛል” ይላል ምንጩ ያልታወቀ የከረመ አባባል፡፡ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ለማለፍ ፈቃደኛ እስካልሆንክ ድረስ የብቃትህን ጥግ ሳታውቀው ታልፋለህ፡፡ የሰው አቅሙና ብቃቱ የሚወጣው በሚያልፍበት አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ነው፡፡

ብዙ ሰዎች አሁን ከድሮው ሕይወታቸው የተሻለ ኑሮን እየኖሩና የአሁኑ ዘመን ከበፊቱ በብዙ እጥፍ እየበለጠ እንኳን፣ “ድሮ ቀረ!” ሲሉ የሚደመጡት የበፊቱ አስቸጋሪ ዘመን በጊዜው ፈትኗቸው ቢሆንም እንኳን ተደብቆ የነበረውን እምቅ ብቃታቸውንና ድብቅ ብርታታቸውን እንዳወጣው ያውቃሉ፡፡ እነዚህ ሰዎች ዛሬ የሆኑትን የሆኑት፣ ዛሬ የሚችሉትን የቻሉት፣ ዛሬ የገባቸው ነገር የገባቸው . . . ከእነዚያ ፈታኝ፣ ነገር ግን ድንቅ አመታት የተነሳ እንደሆነ ውስጣቸው ያውቀዋል፡፡

አንዳንድ ሰዎች አስቸጋሪ ሁኔታዎች ሲገጥማቸው የበለጠ እያዳበሩ የሚሄዱት “ችሎታ” ከዚያ ሁኔታ፣ ስፍራ፣ ግንኑነት … የመሸሽን ችሎታ ብቻ ነው፡፡ ስለዚህ ግሩም የሆኑ “የሽሽት ባለሞያዎች” ወደመሆን ያድጋሉ፡፡ የስራና የትምህርት ዘርፍ ከበድ ሲላቸው እየለወጡ ውስጣቸው ግን ሳይለወጥ፣ የትዳር ሕይወት ችግር ይዞ ሲመጣ የትዳር ጓደኛን እየቀየሩ ባሪያቸው ግን ሳይቀየር፣ መንደር፣ ሰፈርና ሃገር አልመች ሲላቸው እየለወጡ አመለካከታቸው ግን ሳይለወጥ እንደነበሩ ይኖራሉ፡፡

ምን ያህል አስገራሚ ብቃት እንዳለህ ማንም ሰው አያውቀውም፣ አንተው ራስህ እንኳን በቅጡ አታውቀውም፡፡ ይህንን ብቃትህን የሚያወጣው ጉዳይ “ችግር” ይባላል፡፡ ይህ ችግር የሚባል ነገር በሁለት ይከፈላል፣
1) አስፈላጊ ችግርና፣
2) አላስፈላጊ ችግር፡፡

አስፈላጊው ችግር የተለመደውን የሕይወት መስክ ይዘህ ስትጓዝ በተመሳሳይ ሁኔታ የሚያልፍ ሰው ሁሉ የሚጋራው ችግር ነው፡፡ ይህንን ችግር ከመሸሽ ይልቅ ስትጋፈጠው የውስጥህ ብቁ ማንነት ይወጣል፡፡

አላስፈላጊ ችግር በእኛው የጥበብ ጉድለትና የተሳሳተ ውሳኔ የሚመጣው አይነት ችግር ነው፡፡ ይህን ችግር ሽሸው፣ እንዳይከሰትም የምትችለውን ሁሉ አድርግ፡፡ ሆኖም፣ አንዴ ከተከሰተ ግን ከስህተትህ ተማር፣ ውጤቱንም ተጋፈጥ እንጂ ለመደባበቅና ለመሸሽ አትሞክር፡፡

ዛሬ የምታልፍበት ችግር ነገ በብዙ ብቃት የምትወጣበት አስገራሚ እድል እንጂ ዛሬ የምትደክምበት ሁኔታ እንዲሆን አትፍቀድለት፡፡

ኢትዮጵያ
@Ewiketinfilega
@Ewiketinfilega
@Ewiketinfilega
357 viewsEshe Man, 05:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-18 22:16:24 ፍቅርና ጊዜ


ሁሉም አይነት ስሜቶች የሚኖሩበት አንድ ደሴት ነበር፡፡ የደስታ ስሜት፣የመከፋት ስሜት፣ እውቀት እና ሌሎቹ ስሜቶች ፍቅርን ጨምሮ፡፡ አንድ ቀን ታዲያ ደሴቱ ሊሰምጥ እንደሆነና ሁላቸውም ስሜቶች ሊያመልጡ የሚችሉበትን ጀልባ መስራት እንዲችሉ አዋጅ ተነገረ፡፡ በዚህም መሠረት ሁሉም ስሜቶች ጀልባቸውን ሲሰሩ ፍቅር ግን ደሴቱ እስኪ ሰምጥ ድረስ ጀልባ አልሰራም ነበርና ከሊሎቹ ስሜቶች እገዛ ለመጠየቅ ወሰነ፡፡

ሀብታምነት የሚባለው ስሜት በፍቅር በኩል ሲያልፍ “ሀብታም ሆይ ከአንተ ጋ ይዘኸኝ ልትሻገር ትችላለህ?” አለው ፍቅር፡፡ “አይሆንም፡፡ አልችልም በጀልባየ ውስጥ በርካታ ወርቅና መዳብ የያዝኩ በመሆኑ ለአንተ የሚሆን ቦታ የለኝም” ሲል ጥሎት ሄደ፡፡ ፍቅር አቶ ስግብግብን ሲያልፍ ተመለከተውና እንዲረዳው ጠየቀው፡፡ “አልችልም አቶ ፍቅር ጀልባየን ታበላሽብኛለህ አይሆንም ብሎ” ትቶት ሄደ፡፡ አቶ መከፋትን በቅርብ አገኘውና አሁንም ፍቅር አብሮ እንዲያሻግረው ጠየቀው፡፡ “ኦው! ፍቅር አዝናለሁ እኔ ብቻየን ነው መሆን የምፈልገው፡፡” ብሎ አሰናበተው፡፡ ደስታም ፍቅርን አልፎት እየሄደ በጣም በፈንጠዝያ ስሜት ላይ ስለነበር ፍቅር ሲጠራውም መስማት አልቻለም፡፡

ፍቅር ትዕግስቱን እያጣ በመከፋት ስሜት እንዳለ ባጋጣሚ “ፍቅር ና እኔ እወስድሃለሁ” የሚል ድምጽ ሰምቶ ሲዞር የተባረከ አዛወንት ነበር፡፡ “ጊዜው ነው” ወዳጀ ፍቅር ሲል እውቀት የተባለው ስሜት መለሰ፡፡

“ጊዜ ማለት!?” ፍቅር በመደነቅ ጠየቀው “ነገር ግን ለምን ጊዜው ሊረዳኝ ቻለ?” እውቀት ፈገግ እያለ ምክንያቱም “የፍቅርን ዋጋ መረዳት የሚችለው ጊዜ ነው፡፡” ሲል መልስ ሰጠው፡፡

በዚህ ዓለም ፍቅር ብቻ ነው ሠላምንና ታላቅ ደስታን ሊያመጣ የሚችለው፡፡ ባለጸጎች ስንሆን ፍቅርን ካራቅነው፣ ተፈላጊነታችን ሲጨምር ፍቅርን ከዘነጋን፣ ምናልባትም በደስታና በሀዘን ስሜት ስንሆንም ፍቅር ካጣን የማስተዋል ጊዜው ሲደርስ ነው የፍቅር ጥፍጥና የሚታወቀን፡፡

የልባችን ብርሀን የሚበራው በፍቅር ነውና ሁሌም ፍቅርን እናስቀድም፡፡


@Ewiketinfilega
@Ewiketinfilega
110 viewsEshe Man, 19:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-18 18:44:16
ሕይወትን ቀለል ብናደርጋት ኖሮ!



የተወለድነው በሌሎች ሰዎች እርዳታ ነው፡፡
ስማችንን የተቀበልነው ሌሎች ሰዎች ባወጡልን መሰረት ነው፡፡
የገቢ ምንጫችን የሚመጣው ከሌሎች ሰዎች ነው፡፡
ክብርና እውቅና የሚሰጡን ሌሎች ሰዎች ናቸው፡፡
ገላችንን ለመጀመሪያ ጊዜ ያጠቡን ሌሎች ሰዎች ናቸው፣ ለመጨረሻ ጊዜ የሚያጥቡንም ሌሎች ሰዎች ናቸው፡፡
ከዚህ አለም ስንሰናበት ቤታችንና ንብረታችን በሌሎች ሰዎች ይወሰዳል፡፡
እጃችንን ይዘው በመደገፍ መራመድ ያስለመዱን ሌሎች ሰዎች ናቸው፣ በመጨረሻም እጃችንን ይዘው በመደገፍ የሚያራምዱን ሌሎች ሰዎች ናቸው፡፡
በመወለዳችን ምክንያት በደስታ የደገሱና የበሉት ሌሎች ሰዎች፣ ስንሞትም በኃዘን የሚደግሱና የቀብር ስርአታችን የሚከናወነው በሌሎች ሰዎች ነው፡፡

ይህ ሁሉ እውነታ እያለ “ነኝ” እና “አለኝ” በምንለው ነገር የምንመካበት ጉዳይ አይገባኝም፡፡ እስቲ ያወሳሰብናትን ሕይወትን ቀለል እናድርጋትና ለመከባበርና ለመዋደድ ቅድሚያን በመስጠት እንኑር፡፡
ዶ/ር እዮብ ማሞ

@Ewiketinfilega
@Ewiketinfilega
107 viewsEshe Man, 15:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-18 05:13:18
107 viewsEshe Man, 02:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-16 13:34:08
የምንፈልገውን ለማግኘት ብቻ ከመማሰን ያገኘነውን በመውደድና በማመስገን ቀናችንን እናስውብ ፡፡

ከመጸለይህ በፊት ተመስገን በል። ስለሁሉም ነገር አመስግን...በረከቶችህን ቁጠር! ጠዋት ገና ከእንቅልፍህ ስትነቃ....አይኖችህን ስትገልጥ.....አየሩን ስትተነፍስ <<ተመስገን>> በል!!!...ሞተህ ልታድር ትችል ነበርና!!! ደግሞ ከአልጋህ ወርደህ መሬት ስትቆም……‹‹ተመስገን>> በል! በሆነ ምክንያት የአልጋ ቁራኛ ሆነህ ልትቀር ትችል ነበርና!!! ውለህ ስትገባ ተመስገን በል፣ ብዙዎች እንደወጡ የቀሩ አሉና።

በየትኛውም መንገድህ ላይ አመስግን። ምስጋና ቢስ አንደበቶች ልመናን ሲያሻግሩ ለዛቸውን ያጣሉ!

( ደራሲ ስብአት ገ/ እግዚአብሔር)

ውብ ዛሬ!!!

@Ewiketinfilega
@Ewiketinfilega
121 viewsEshe Man, 10:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ