የሰርጥ አድራሻ:
ምድቦች:
ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች:
83.70K
የሰርጥ መግለጫ
This is Ministry of Education's Official Telegram Channel.
For more updates please visit www.facebook.com/fdremoe
Ratings & Reviews
Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.
5 stars
3
4 stars
0
3 stars
0
2 stars
0
1 stars
0
የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 7
2023-12-09 17:16:44
"በትብብርና አለም አቀፍ ተሳትፎ የሀገራችንን የአካዳሚክ ጉዳዮች ማስተዋወቅ ይገባል" ዶ/ር ሀብታሙ አበበ የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት
.............................................
ህዳር 28/2016 ዓ.ም (ትምህርት ሚኒስቴር) የከፍተኛ ትምህርት የኮሙዩኒኬሽንና አለም አቀፍ ግንኙነት አመራሮች በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የኮሙኒኬተሮች ፎረም እያካሄዱ ነው።
በፎረሙ ላይ የተገኙት የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ሀብታሙ አበበ ይህ መድረክ በትምህርት ዘርፉ እየተሰሩ ያሉ ስራዎች ላይ ልምድ ለመለዋወጥ ያግዛል ብለዋል።
በተለይም በአለም አቀፍ የአካዳሚክ ምህዳር ላይ የትብብር ድልድይ ለመገንባት የህዝብ ግንኙነትና አለም አቀፍ ክፍሎች ሚና የጎላ መሆኑን አንስተዋል።
በዚህም ሀገራችንን በአካዳሚክ ጉዳዮች በአለም አቀፍ ደረጃ ለማስተዋወቅ የተጠናከረ ህዝብና አለም አቀፍ ግንኙነት ሥራ መሥራት እንደሚጠበቅም ተናግረዋል።
በተጨማሪም ይህ መድረክ ዩኒቨርሲቲዎች ያላቸውን ተሞክሮና አዳዲስ ስልቶች ላይ እርስ በርስ ልምድ ለመለዋወጥ እንዲሁም የትምህርት ሚኒስቴርን የሪፎርም አጀንዳዎች በሚገባ በመረዳት ለማህበረሰቡ የምናስተዋውቅበትን እድል ይፈጥራልም ብለዋል።
ሙሉ ዜናው
።https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid0gQpNhitnjifce9LQgK76YR4wocLdrzV5XQTAguMzUG7WCCZeJs9RrJ3QwDFHLVZKl&id=100064682287722&mibextid=9R9pXO
16.9K views14:16
2023-12-08 03:46:21
ማስታወቂያ
የሁለተኛ ደረጃ ትምህርትን በእንግሊዝኛ ቋንቋ መማራቸውን የሚገልጽ ደብዳቤ (Letter of proficiency) እንዲጻፍላቸው ለሚፈልጉ ተገልጋዮች ወደ ትምህርት ሚኒስቴር ሲመጡ ማሟላት የሚጠበቅባቸው መሥፈርቶች: -
1. አሥራ ሁለተኛ ክፍል ማጠናቀቃቸውን የሚገልጽ ኦሪጅናል ሰርተፊኬትና የማይመለስ አንድ ኮፒ፣
2. በቀድሞው የትምህርት ፖሊሲ 10ኛ ክፍል አጠናቀው የመሰናዶ ትምህርት (ፕሪፓራቶሪ) ያላጠናቀቁ ከሆነ 10ኛ ክፍል ማጠናቀቃቸውን የሚገልጽ ኦሪጅናል ሰርተፊኬትና የማይመለስ አንድ ኮፒ፣
3. አመልካቾች ማንነታቸውን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ ወይም ፓስፖርት ወይም መንጃ ፈቃድ ከማይመለስ አንድ ኮፒ ጋር ማቅረብ የሚጠበቅባቸው ሲሆን አገልግሎቱ የሚሰጥባቸው ቀናት ሰኞ እና ሐሙስ በሥራ ሰዓት መሆኑን እንገልጻለን፡፡
ትምህርት ሚኒስቴር
18.0K views00:46
2023-12-06 19:14:11
የትምህርት ሚኒስቴር አመራሮችና ሰራተኞች 18ኛውን የብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን አከበሩ
……………………………………………………………………………………………………………………………………………………………………………………….
ህዳር 26/2016 ዓ/ም (ትምህርት ሚኒስቴር) የትምህርት ሚኒስቴር አመራሮችና ሰራተኞች 18ኛውን የብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን አከበሩ።
በትምህርት ሚኒስቴር የሚኒስትር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጌታቸው ተፈራ በበዓሉ ላይ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር የብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ቀን የኢትዮጵያዊነት ሚዛንን በጠበቀና የአንድነታችንን ገመድ ባጠናከረ ሁኔታ ሊከበር ይገባል ብለዋል።
የብሄር ብሄረሰቦች ቀን ብሄር፣ ብሄረሰቦችና ህዝቦች መብትና እኩልነታቸው ህገ መንግስታዊ እውቅና እና ጥበቃ ያገኘበት ታሪካዊ ዕለት መሆኑን ጠቅሰው ራስን ማስተዳደር መብትን ጨምሮ ባህልና ቋንቋቸው በማሳደግ ሰፊ ርቀት መጓዝ መቻላቸውን ኃላፊው ገልጸዋል።
“ብዝሀነትና እኩልነት ለአገራዊ አንድነት “ በሚል መሪ ቃል በተከበረው በዓል ላይ በትምህርት ሚኒስቴር የማህበራዊ ሳይንስ ስርዓተ ትምህርት ዴስክ ኃላፊ አቶ ዑመር ሰይድ በህገ መንግስትና በህብረብሄራዊ ፌዴራሊዝም ላይ ያተኮረ የመወያያ ሰነድ አቅርበው በተሳታፊዎች ውይይት ተደርጎበታል፡፡
ተጨማሪ መረጃዎችን በሚከተሉት ማስፈንጠሪያዎች ያግኙ፡-
በፌስቡክ -https://www.facebook.com/fdremoe/
በቴሌግራም -https://t.me/ethio_moe
በትዊተር - http://twitter.com/fdremoe
በሊንክዲን - https://www.linkedin.com/.../ministry-of-education-ethiopia
በዌብሳይት - www.moe.gov.et
ይከታተሉ
19.5K views16:14
2023-11-28 14:16:45
17.5K views11:16
2023-11-28 13:53:27
በእውቀት የበለጸገ ማህበረሰብ ለመፍጠር ብዙ መሥራት እንደሚገባ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ አስገነዘቡ
..................................................................................
ህዳር 18/2016 ዓ.ም (ትምህርት ሚኒስቴር) 32ኛው አገር አቀፍ የትምህርት ጉባዔ በጅግጅጋ እየተካሄደ ይገኛል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ በጉባዔው መክፈቻ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ዕውቀት የሚጎለብተው በከፍተኛ ትብብርና መደጋገፍ ነው።
በመሆኑም ዕውቀት የበለጸገ ማህበረሰብ ለመፍጠር እንደአገር ገና ብዙ መሥራት እንደሚገባ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ አስገንዝበዋል።
አሁን ባለው ሁኔታ መቀጠል እንደማይቻል የጠቆሙት ሚኒስትሩ ለሚቀጥለው ትውልድ የተሻለ ሁኔታ ለመፍጠር የሚያስችል ዕውቀት መስጠት ይገባል ብለዋል።
ሚኒስትሩ አክለውም የትምህርት ጉባዔው የተዘጋጀው ለሥራ ፣ለዕውቀት ፣ አብሮ ለመኖርና ለመሣሰሉት ያለንን አመለካከት ለመቀየር መሆኑን ጨምረው ገልጸዋል።
ሙሉ ዜናውን
https://www.facebook.com/100064682287722/posts/pfbid02smZknTxfdvCUr1ZQPHAvU9YtRJhmG98W6VLK8CGg6FxYi41XN2d4a8B6m6hTCQZMl/?mibextid=9R9pXO
የትምህርት ሚኒስቴር ዜናዎችን
በፌስቡክ -https://www.facebook.com/fdremoe/
በቴሌግራም -https://t.me/ethio_moe
በትዊተር - http://twitter.com/fdremoe
በሊንክዲን - https://www.linkedin.com/.../ministry-of-education-ethiopia
በዌብሳይት - www.moe.gov.et
ይከታተሉ
18.0K views10:53
2023-11-27 15:09:01
የስራና ተግባር ትምህርት በቀጣይ ዓመት ወደ ትግበራ ለመግባት ዝግጅት እየተካሄደ መሆኑ ተገለፀ።
.............................................
ህዳር 17/2016 ዓ.ም (ትምህርት ሚኒሰቴር ) 32ኛው የትምህርት ጠቅላላ ጉባኤ አካል የሆነው የዘርፎች ትይዩ ጉባኤ በሶማሌ ብሄራዊ ክልል ጅግጅጋ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል፡፡
የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ አየለች እሸቴ የጉባኤው ዋና አላማ በእቅድ ትግበራ ወቅት የተገኙ መልካም ተሞክሮዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ እና ባጋጠሙ ችግሮች ላይ የመፍትሄ አማራጮችን ለመቀየስ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡
አዲሱ የአጠቃላይ ትምህርት ስርዓተ ትምህርት ከ1ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ወደ ሙሉ ትግበራ የተገባ መሆኑ እና የስራና ተግባር ትምህርት በቀጣይ ዓመት ወደ ትግበራ ለመግባት ዝግጅት እየተካሄደ መሆኑንም ሚኒስትር ዴኤታዋ ገልጸዋል፡፡
የትምህርት ጥራት ችግሮችን ለመቅረፍ የተለያዩ የለውጥ መርሃ-ግብሮች ተቀይሰው ወደ ተግባር መግባታቸውንም ጠቁመዋል።
የበጀት እጥረት፣ የስምሪትና መልካም አስተዳደር ችግሮች፣ የትምህርት ቤት ምገባ መርሃ ግብር በሚፈለገው መልኩ ተግባራዊ ያለመሆን፣የተማሪዎች ውጤት ዝቅተኛ መሆኑ እና የመሳሰሉት ችግሮች የትምህርት ስርዓቱ የወቅቱ ፈተናዎች መሆናቸውን አብራርተዋል፡፡
በመድረኩ የሶማሌ ብሄራዊ ክልል ትምህርት ቢሮ ሃላፊ አቶ አብዱላሂ አብዲ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
ሙሉ ዜናው
https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid08Ni8hmbg2MDHq2WXLz93LB4d4FuYSJzG2yFdruADXku2jMPAEeTgsCEAy2GowF7Gl&id=100064682287722&mibextid=9R9pXO
19.6K views12:09
2023-11-27 14:27:09
በቀጣይ ሁለት ዓመታት በተልዕኮና ትኩረት መስካቸው የተለዩ 9 ዩኒቨርስቲዎችን ወደ ራስ ገዝ ደረጃ ለማሻገር እየተሰራ ነው:- ትምህርት ሚኒስቴር
...............................................................................
ህዳር 17/2016 ዓ.ም (ትምህርት ሚኒስቴር) የከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ኮራ ጡሽኔ
እንደገለጹት በቀጣይ ሁለት ዓመታት 9 ዩኒቨርስቲዎችን ራስ ገዝ ለማድረግ እየተሰራ ይገኛል።
በ32ኛው የትምህርት ጉባኤ ቅድመ ጉባኤ ትይዩ መድረክ መክፈቻ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጥራት ያለው ትምህርት በማቅረብ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ቴክኖሎጁ የሚጠቀም ፣ የሚመራመርና በሥነምግባር የታነጸ ዜጋ መፍጠር እንደሚጠበቅባቸውም ሚኒስትር ዴኤታው አስገንዝበዋል።
የጉባዔው ዓላማ በከፍተኛ ትምህርቱ ዘርፍ የተመዘገቡ ስኬቶችን ፣ ያጋጠሙ ችግሮችና የወደፊት አቅጣጫዎች ላይ በመወያየት በቀጣይ ስለሚወሰዱ የእርምትና የለውጥ እርምጃዎች ላይ የጋራ ግንዛቤና አቋም ለመያዝ መሆኑን ጠቁመዋል።
የጅጅጋ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር በሽር አብዱላሂ ባስተላለፉት የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት ጅግጅጋ ዩኒቨርስቲ በአፕላይድ ዩነቨርስቲ የተልዕኮና ትኩረት መስክ ለይቶ በተፈጥሮ ሀብት እርብቶአደርና እንስሳት ልማት እንዲሁም በምግብ ዋስትና ቢዝነስና ኢኮኖሚክስ መስክ እየሠራ መሆኑን ተናግረዋል።
ሙሉ ዜናው
https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid02S887Ytq9QQBn55bzT54gyCDpavzUk6oBsQKyC5N9AwS293A1Wm6HGZU7cVGqsCjzl&id=100064682287722&mibextid=9R9pXO
18.7K views11:27
2023-11-23 21:37:33
ከ10 ነጥብ 6ሚሊዮን በላይ መጻህፍት ለክልሎች ተከፋፈሉ
...................................................
ህዳር 13/2016 ዓ.ም (ትምህርት ሚኒስቴር) በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት መሠረት የተዘጋጁ ከ10 ነጥብ 6 ሚሊዮን በላይ መጻህፍት ለክልሎች ተከፋፍለዋል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ለጋዜጠኞች እንደገለጹት ወደ አገር ውስጥ የገባ 10 ሚሊዮን 649 ሺ የ2ኛ ደረጃ መጽሀፍት ለክልሎች ተከፋፍለዋል።
በጅቡቲና በደረቅ ወደብ የሚገኝ ተጨማሪ 10 ሚሊዮን መጻሕፍትም እስከ መጪው ታህሳስ ወር አጋማሽ ድረስ ተጓጉዞ ለክልሎችእንደሚሰራጭ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ተናግረዋል።
40 ነጥብ 1 ሚሊዮን ዶላር ወጥቶባቸው ህትመታቸው የተጠናቀቁት መጻህፍት ከ9ኛእስከ 12ኛ ክፍል ለማስተማሪያነትና ለመምህሩ መምሪያነት የሚያገለግሉ ናቸው።
የመጽሀፍት ስርጭቱ በአገሪቱ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ያለውን የአዲሱ ስርዓተ ትምህርት የመማሪያ መጻሕፍት እጥረት እንደሚያቃልለው ሚኒስትሩ ጠቅሰዋል።
የመጻሕፍት እጥረትን ለመፍታትም አሁን ከታተሙት የ20 ነጥብ 7 ሚሊየን መጽሐፍት በተጨማሪ በቀጣይ ተጨማሪ መጻሕፍትን ለማሳተም ዝግጅት እየተደረገ መሆኑንም ፕሮፌሰር ብርሃኑ አብራርተዋል።
ተጨማሪ መረጃዎችን በሚከተሉት ማስፈንጠሪያዎች ያግኙ፡-
በፌስቡክ -https://www.facebook.com/fdremoe/
በቴሌግራም -https://t.me/ethio_moe
በትዊተር - http://twitter.com/fdremoe
በሊንክዲን - https://www.linkedin.com/.../ministry-of-education-ethiopia
በዌብሳይት - www.moe.gov.et
ይከታተሉ
18.2K views18:37
2023-11-23 16:25:47
የትምህርት ሚኒስቴር መረጃዎችን በሚከተሉት ማስፈንጠሪያዎች ያግኙ፡-
በፌስቡክ -https://www.facebook.com/fdremoe/
በቴሌግራም -https://t.me/ethio_moe
በትዊተር - http://twitter.com/fdremoe
በሊንክዲን - https://www.linkedin.com/.../ministry-of-education-ethiopia
በዌብሳይት - www.moe.gov.et
ይከታተሉ
20.4K viewsedited 13:25