Get Mystery Box with random crypto!

Ministry of Education Ethiopia

የሰርጥ አድራሻ: @ethio_moe
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 83.70K
የሰርጥ መግለጫ

This is Ministry of Education's Official Telegram Channel.
For more updates please visit www.facebook.com/fdremoe

Ratings & Reviews

5.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

3

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 5

2024-01-24 12:51:49
#ማ ስ ታ ወ ቂ ያ

የመውጫ ፈተና መመዝገቢያ ጊዜ እስከ 20/2016ዓ.ም መራዘሙን ስለማሳወቅ

በ2016 ዓ.ም የመውጫ ፈተና ለመፈተን የምዝገባ ጊዜው ጥር 08/2016 ዓ.ም ጀምሮ ጥር 15/2016 ዓ.ም እንደሚጠናቀቅ መጠቀሱ የሚታወሰ ነው።

ይሁን እንጂ በተፈታኞች ጥያቄ መሰረት የምዝገባ ጊዜው እስከ ጥር 20/2016 ዓ.ም የተራዘመ መሆኑን እያሳወቅን ሌሎች ሁኔታዎች ግን ቀደም ሲል በተገለጸው አግባብ የሚከናወኑ መሆኑን እናሳውቃለን።
======================
የመውጫ ፈተና በድጋሚ ለምትፈተኑ አመልካቾች በሙሉ

ከ2015 የትምህርት ዘመን ጀምሮ በሁሉም በቅድመ ምረቃ ፕሮግራሞች ለእጩ ተመራቂ ተማሪዎች የከፍተኛ ትምህርት የመውጫ ፈተና እየተሰጠ መሆኑ ይታወቃል፡፡ በ2016 ዓ.ም አጋማሽ ላይ የመውጫ ፈተናን ለመፈተን በመጠባበቅ ላይ ያላችሁ ተፈታኞች በሙሉ ፈተናው ከጥር 27- የካቲት 1/2016 ዓ.ም የሚሰጥ ይሆናል፡፡

ሙሉ ማስታወቂያው

https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=pfbid02fonYtnk7WiKJxmE5jhrbK6D4Hwx6rkrQTTR62bUdWGMebLHHc369kutmGZkENvPyl&id=100064682287722&mibextid=9R9pXO
21.5K views09:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-01-23 16:05:36
የመምህራንና ትምህርት ቤት አመራሮችን የዲጂታል ቴክኖሎጂ አቅም ለመገንባት እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ፡፡
======================
ጥር 14/2016 ዓ.ም (ትምህርት ሚኒስቴር) በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ለሚገኙ መምህራን እና የትምህርት ቤት የአመራሮችን የዲጂታል ቴክኖሎጂ አቅም ማሳደግን ኢላማ አድርገው በዓለም ባንክ እገዛ የተገዙ 3,790 ታብሌቶች ርክክብ ተደረጓል፡፡

በትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ የመምህራንና ትምህርት አመራር መሪ ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ሙሉቀን ንጋቱ በርክክብ ስነስርዓቱ ላይ የተሰራጩት ታብሌቶች የትምህርት ስርዓቱን በቴክኖሎጂ በመደገፍ በኩል ትልቅ እገዛ እንዳላቸው ገለጸዋል።

ዶ/ር ሙሉቀን አክለዉም ታብሌቶቹ በተመረጡ ጉድኝት ማእከላት ትምህርት ቤቶች በኩል 18,000 የሚሆኑ የ1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን ተደራሽ እንደሚያደርጉ ጠቅሰው ለታለመለት ዓላማና ተግባር ብቻ እንዲውሉ አሳስበዋል፡፡

በትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት ልማት ዘርፍ የመምህራንና ትምህርት አመራር ዴስክ ኃላፊ የሆኑት ወ/ሮ አሰግድ መሬሳ በበኩላቸው የታብሌቶቹ ስጦታ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት መምህራን የዲጂታል ቴክኖሎጂ ክህሎት በማሻሻል መምህራን የመማር ማስተማር ተግባርን በዲጂታል ቴክኖሎጂ አስደግፈው አንዲሰጡ ለማስቻል፣ የአንደኛ ደረጃ ትምህርት መምህራንና ትምህርት ቤት አመራሮች አጫጭር የስራ ላይ አቅም ማጎልበቻ ስልጠናዎችን በዲጂታል ቴክኖሎጂ ለማገዝና አጠቃላይ የመምህራን ስልጠና ስርዓትን ዲጅታላይዝ ለመድረግ ያለመ ነው ብለዋል።

በርክክቡ ወቅትም ስራው ከዓለም ባንክ ጋር በጋራ እየተሰራ መሆኑንና በ2015 ዓ.ም 47 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶችን ማእከል ያደረገ 1000 ታብሌቶች ለክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች የተሰራጩ መሆኑ ተገልጿል፡፡
13.5K views13:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-01-19 21:20:40
13.2K views18:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-01-11 11:21:49
የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር ከኮሪያ ጋር በትምህርት ኢንፎርሜሽን ልውውጥና ትብብር ላይ የስምምነት ሰነድ ተፈራረመ ፡፡
..................................... // ...............................
ጥር 2/2016 ዓ.ም (ትምህርት ሚኒስቴር) የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር ከኮሪያ ጊዮንግሳንግቡክ-ዶ (Geongsangbuk-do) ትምህርት ቢሮ ጋር በትምህርት ኢንፎርሜሽን ልውውጥና ትብብር ዙሪያ በጋራ ለመስራት የሚያስችል የትብብር መግባቢያ ሰነድ ስምምነት ተፈራርሟል፡፡

የትብብር ስምምነቱ በሁለቱ ሃገራት መካከል ከ20016-2017 ዓ.ም የሚደረገውን የትምህርት ኢንፎርሜሽን ልውውጥና ትብብርን የተመለከተ ነው።
ስምምነቱ በሀገራቱ መካከል ያለውን የወዳጅነትና ድጋፍ ከማጠናከሩ ባሻገር በዲጂታል የትምህርት ስትራቴጂና የማስፈጸሚያ ዕቅድ አተገባበር እንዲዳብር ለማበረታታት ያስችላል ተብሏል፡፡

በትብብር ስምምነት ሰነዱ ላይ የአይሲቲ መሳሪያዎችን ማቅረብና ለተመረጡ መምህራን ከትምህርታዊ መረጃ አሰጣጥ ጋር የተያያዘ ስልጠና መስጠት የኮሪያ መንግስትን የሚመለከቱ መሆኑና የስልጠና ተሳታፊዎችን መምረጥን በተመለከተ የትምህርት ሚኒስቴርን የሚመለከቱ መሆናቸውን ተካተውበታል፡፡

የኢፌዲሪ ትምህርት ሚኒስቴር ሚንስትር ዴኤታ ወ/ሮ አየለች እሸቴ እና የጊዮንግሳንግቡክ-ዶ ቢሮ የትምህርት ዘርፍ አስተዳዳሪ ሊም ጆንግ-ሲክ በእለቱ ተገኝተው ስምምነቱን ፈርመዋል፡፡
14.6K views08:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-01-09 17:16:28
17.6K views14:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-01-06 16:52:32
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮችና የትምህርቱ ማህበረሰብ እንኳን ለገና በዓል በሰላም አደረሳችሁ! በዓሉ የሰላምና የደስታ እንዲሆን እንመኛለን።

ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ
የትምህርት ሚኒስትር
25.6K views13:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-01-03 11:03:23
15.0K views08:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-01-01 08:26:15
15.4K views05:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-12-31 09:51:58
20.5K views06:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-12-30 10:46:25
ብዝኃነትን መኖር በሚል መሪ ሐሳብ የአብሮነት ቀን ለስድስት ቀናት መከበር ጀምሯል።
.............................................
ታህሳስ 20/2016 ዓ.ም (ትምህርት ሚኒስቴር) እ.አ.አ. በ1995 የተባበሩት መንግስታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት ፦ ዩኔስኮ ኅዳር 6 ቀንን  ዓለም አቀፍ የአብሮነት (Tolerance) ቀን እንዲኾን ዐውጇል፡፡

የቀኑ መታወጅ ዓላማ በኅብረተሰቡ ውስጥ የአብሮነትን ጥቅም ግንዛቤ ለመፍጠርና መቻቻል ያለዉን ፋይዳ ማስገንዘብ ነው፡፡

በኢትዮጵያም ብዝኃነትን የሚያከብር፣ አብሮነትን ገንዘብ ያደረገ፣ ኃላፊነት የሚሰማዉ ትውልድ ለማፍራት የተጀመረዉን ጥረት ለማገዝ፣ ማኅበራዊ ዕሴቶቻችንን ለማሳደግና ለለውጥ ዝግጁ ዜጋና  ኅብረተሰብ ለመፍጠር ተቻችሎ መኖር አንዱ ለአንዱ አስፈላጊዉ አንደኾነ ማመንን ለማስረጽና ግንዛቤ ለማሳደግ ቀኑ ይከበራል፡፡ 

ዘንድሮ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ26ኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ለ14ኛ ጊዜ የሚከበረዉ ዓለም አቀፉ የአብሮነት ቀን "ብዝኃነትን መኖር!" በሚል መሪ ሐሳብ ከታኅሣሥ 20-25 ቀን 2016 ዓ.ም እየተከበረ ይገኛል።

የአብሮነት ሳምንቱ በልዩ ልዩ ኹነቶች እንደሚከበር ከመርሐ ግብሩ መረዳት ተችሏል።

የበዓሉን አከባበር ባህልና ስፖርት ሚኒስቴር ከተለያዩ የፌዴራል ተቋማትና ከሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጋር በመኾን ያስተባብራል።

ተጨማሪ መረጃዎችን በሚከተሉት ማስፈንጠሪያዎች ያግኙ፡-

በፌስቡክ -https://www.facebook.com/fdremoe/
በቴሌግራም -https://t.me/ethio_moe
በትዊተር - http://twitter.com/fdremoe
በሊንክዲን - https://www.linkedin.com/.../ministry-of-education-ethiopia
በዌብሳይት - www.moe.gov.et
ይከታተሉ
13.8K views07:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ