የሰርጥ አድራሻ:
ምድቦች:
ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች:
119
የሰርጥ መግለጫ
ይህ ኢስላማዊ ካሊግራፊ ስራዎች የሚቀርቡበት ልዩ ቻናል ነው።
ለስጦታዎች የፍሬም ስራዎችን ለማሰራት ከፈለጉ ይቀላቀሉን።
"ያ አላህ ለሰጠከኝ ፀጋ ሁሉ አመሰግንሀለው!"
for any comment :- @Eluna55
Ratings & Reviews
Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.
5 stars
0
4 stars
1
3 stars
0
2 stars
0
1 stars
1
የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች
2022-04-23 09:31:46
◕ ‿ ◕ ረመዷን-22 ◕ ‿ ◕
┊ ┊ ┊ ┊
┊ ┊ ┊
┊ ┊
┊
*•.¸ ¸.•*አዝካሩ-ሰባህ*•.¸ ¸.•*
አልሃምዱሊላህ..... አዲስ ንጋት። የዒባዳ ቀን.... አዝካርና ጀምበር
ያ ሸሂድ! አጠያየቅ አናውቅምና ካስተማርከን እንጠይቅሃለን
رَّبَّنَآ إِنَّنَا سَمِعْنَا مُنَادِيًا يُنَادِى لِلْإِيمَٰنِ أَنْ ءَامِنُوا۟ بِرَبِّكُمْ فَـَٔامَنَّا رَبَّنَا فَٱغْفِرْ لَنَا ذُنُوبَنَا وَكَفِّرْ عَنَّا سَيِّـَٔاتِنَا وَتَوَفَّنَا مَعَ ٱلْأَبْرَارِ
«ጌታችን ሆይ! እኛ በጌታችሁ እመኑ በማለት ወደ እምነት የሚጠራን ጠሪ ሰማን፡፡ አመንም፡፡ ጌታችን ሆይ! ኃጢአቶቻችንንም ለኛ ማር፡፡ ክፉ ሥራዎቻችንንም ከኛ አብስ፡፡ ከንጹሖቹም ሰዎች ጋር ግደለን፤» [አሊ-ዒምራን 193]
ሰባሁኩም ኑር
*•.¸ ¸.•* *•.¸ ¸.•* *•.¸ ¸.•* *•.¸ ¸.•*
@elunacalligraphy
75 viewsedited 06:31
2022-04-19 09:39:31
◕ ‿ ◕ ረመዷን-18 ◕ ‿ ◕
┊ ┊ ┊ ┊
┊ ┊ ┊
┊ ┊
┊
*•.¸ ¸.•*አዝካሩ-ሰባህ*•.¸ ¸.•*
አልሃምዱሊላህ..... አዲስ ንጋት። የዒባዳ ቀን.... አዝካርና ጀምበር
ያ ሰመድ! አጠያየቅ አናውቅምና ካስተማርከን እንጠይቅሃለን
رَبَّنَآ أَفْرِغْ عَلَيْنَا صَبْرًا وَثَبِّتْ أَقْدَامَنَا وَٱنصُرْنَا عَلَى ٱلْقَوْمِ ٱلْكَٰفِرِينَ
«ጌታችን ሆይ! በእኛ ላይ ትዕግስትን አንቧቧ፤ ጫማዎቻችንንም አደላድል፤ በከሓዲያን ሕዝቦችም ላይ እርዳን» [አል-በቀራህ 50]
ሰባሁኩም ኑር
*•.¸ ¸.•* *•.¸ ¸.•* *•.¸ ¸.•* *•.¸ ¸.•*
@elunacalligraphy
92 views06:39
2022-01-29 08:58:46
መልካም ቅዳሚት!
@elunaaclligraphy || ፍቅር ሰባኪ TemUd
176 viewsedited 05:58
2022-01-20 07:38:49
ለዚህ ነበር?
.
(#ፈይሠል_አሚን)
.
የዘላለም ያህል ረዝሞ. . .
ዘጠኝ ወር አግቶኝ፤
ዘንቶ ለመቀመጥ፣
መወለድ አጓጉቶኝ፤
ሆዷን እረግጣለሁ፣
እጋላበጣለሁ. . .
"ውለጂኝ!" እላለሁ።
.
ማሕፀን ውስጥ አልቀረሁ፣
ተወለድኩ. . .
ተሰወርኩ!
.
ደርሶ ተከፈተ፣የመዓሲያው በር፣
"ኑሮ" በሚሉት የብላሽ አጎበር፣
በከረፋው ቀንበር፣
ታስሬ ልሰበር፣
ሆዷን የረገጥኩት፣ለዚህች ሕይወት ነበር?
.
@elunacalligraphy
172 viewsedited 04:38
2022-01-20 07:38:49
@elunacalligraphy
134 views04:38
2022-01-19 21:43:03
የሰው ልብ አለቅልቀው ባደባባይ የሚያሰጡትን አይቼ ስለነበር በሚፈርዱብሽ ውስጥ እንባሽ ሲንቆረቆር አራሰኝ። እብድ ነች! ብለው በሰንሰለት የጠፈነጉሽ ያሳበዱሽ እንደሆኑ አብሮሽ የተኮራመተው ሰንሰለት በድርብርብ መሰላሎቹ ፅፎት አነበብኩ። አይንሽ ብትስቂም ብታለቅሺም እንደሚያምሽ ያሳብቃል። የህመምሽ ርዝመት ከፀጉርሽ ይበልጣል። ያሳመሙሽ ሰዎች ጨክነውብሽ ቁልቁል እንጂ መቼ ያዩሻል። ኣንቺ መታገል ያቆምሽ ይመስላል ግና ሩቅ ነሽ። አልቅሰሽ አታወጪው፣ ታዝኖልሽ አትድኚው ህመም ቀብረሻል። የህመም ምናኔ ያውቁ ይሆን? ፍላጎትሽ ውስጥ ስመነኩስ አወቅኩት። ሰዎችን ሁሉ በጅምላ እንዳትጠዪ ለምንም አስበው ይስሩት ብቻ ኣንዳንድ ሰዎች አንቺን ከፍ አድርጎ የሚያይ እኔን አሻንጉሊት ትተውልሻል። ተንጋልዬ ሳይሽ ምን እንደሚሰማኝ ሕያዋን መች ያውቃሉ። ከእብድ የተቀመጠ ግዑዝ አሻንጉሊት ብቻ አይደል የምመስላቸው? ግን እንደኔ ኣንዴ እንኳ አግዝፈውና ከፍ አድርገው ቢያዩሽ ሊቀልሽ ይችል ነበር። ባንቺም በኔም ጨከኑ ኣንቺ የምታዪው እኔም የማየው ለየቅል። አሻንጉሊትሽ ነኝ እባክሽ ኣንዴ አንሺኝና እንደ እብድ እንኳ እያየሽኝ ፈገግ በይ! ሕያው ነን የሚሉትን አትጠብቅያቸው ተያቸውና ግዑዛንን እያየሽ አውሪ! ከእግርሽ ስር ተንጋልዬ ከፍ አድርጌ የማይሽ፣ በህመምሽ ውስጥ መንኜ በፍላጎትሽ የመነኮስኩ አሻንጉሊት ነኝ!
(አብዱልሀኪም ሰፋ)
:
@elunacalligraphy
144 viewsedited 18:43
2022-01-17 17:26:41
" ከራስ ጋር ንግግር "
(አብዱልሀኪም ሰፋ)
:
<< አፍቃሪ እንደሆንሽ ብዙ በመሰባበርና በመጎዳት ማረጋገጥ አይጠበቅብሽም። እንቆቆ ትዝታሽን አታንቆለጳጵሺው። ግዴለሽም ተረመጂ! >>
:
@elunacalligraphy
122 views14:26
2022-01-14 08:05:09
ያ ረብ አስደስተን፣
ያስደሰተንንም አስደሰት፣
ተደስተን ማየት የሚፈልጉትንም አስደስት፣
በኛ መደሰት የተደሰቱትንም አስደስት፣
#መልካም_ጁምዐ!
@elunacalligraphy
134 viewsedited 05:05
2022-01-12 20:29:51
፨ "ወቁሉ ሊናስ ሑስነን" ይላል ቁርአናችን።
፨ 'ለሰዎች መልካምን ተናገሩ' ማለት ነው።
፨ ነቢዩም 'በአላህ እና በመጨረሻው ቀን ያመነ መልካም ይናገር አልያም ዝም ይበል።' ይላሉ።
፨ ከአንደበታችን የሚወረወር መልካም ቃል የደከመን ያበረታል፣ የታመመን ይፈዉሳል።
፨ ዱንያ ላይ ያለ ሰው ሁሉ ቁስለኛ ነው፣ ለሰው የማያሳየው የተጎዳ ጎን አለው፣
፨ የተጎዳን አይዞህ በሉ፣ የቆሰለን አክሙ፣
፨ መናገር ባትችሉ እንኳን የመልካም ተናጋሪዎችን መልካም በማስተላለፍ በሌሎች አንደበት መልካምን ተናገሩ፣
፨ ቀኑን በብርቱ ትውሉ ዘንድ ማለዳ፣ ለሊቱን በተስፋ ታድሩ ዘንድ ምሽት ላይ አላህ ያስቻለኝን ያህል እናገራለሁ።
ጌታዬ የንግግር ጥበብን ያስተምረኝ ዘንድ እለምነዋለሁ።
መልካም ምሽት
elunacalligraphy
135 views17:29
2022-01-11 19:07:05
Channel photo updated
16:07