Get Mystery Box with random crypto!

Eluna Calligraphy and Islamic posts

የቴሌግራም ቻናል አርማ elunacalligraphy — Eluna Calligraphy and Islamic posts E
የቴሌግራም ቻናል አርማ elunacalligraphy — Eluna Calligraphy and Islamic posts
የሰርጥ አድራሻ: @elunacalligraphy
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 119
የሰርጥ መግለጫ

ይህ ኢስላማዊ ካሊግራፊ ስራዎች የሚቀርቡበት ልዩ ቻናል ነው።
ለስጦታዎች የፍሬም ስራዎችን ለማሰራት ከፈለጉ ይቀላቀሉን።
"ያ አላህ ለሰጠከኝ ፀጋ ሁሉ አመሰግንሀለው!"
for any comment :- @Eluna55

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-01-10 07:00:12 የማለዳ ማስታወሻ #126
.
አልወደቅሽም፣ዝቅ ብለሽ እየተማርሽ ነው። አላጣሽም፣ ገና የምታገኚው ተደብቆብሽ እየፈለግሺው ነው።
አልጠፋሽም፣ በማታውቂው አቋራጭ እየተጓዝሽ ነው።
መድረስ አላቃተሽም፣ መጀመርሽን ልብ ስላላልሺው የት እንደደረስሽ ጠፍቶሽ ነው። የያዝሺው ሁሉ አልተበተነብሽም፣ በቦታው ሊቀመጥ ከእጅሽ ወጥቶ ነው።
.
ስንፍናሽ አንዲት ብቻ ናት። ለሚፈጠረው እንቆቅልሽ ሁሉ በጎ ግምት (መልስ) አለማበጀት!!! "ሁሉም ለበጎ ነው" ብለሽ አሳድገሽን የለ?
.
#ኢትዮጵያ
.
(#ፈይሠል_አሚን)
.

@elunacalligraphy
124 views04:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-09 20:24:17 @elunacalilgraphy
115 viewsedited  17:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-08 21:39:42 ዛሬ አልቅሰን ነገ እንስቃለን
ዛሬ ታመን ነገ እንረሳለን
ዛሬ በጣም አዝነን ነገ ደስታ ይተናነቀናል
ምንም ሚቆይ ሚዘውትር ነገር የለም
ዱንያ ላይ ነን ሁሉም ያልፋል…
አኼራ የሚባል ዘውታሪ ሀገር አለብን
ዋና ቁም ነገር ለዛ ቤት መዘጋጀት ውዶቼ
ያንን ማሳመር ነው ያ ዘውታሪ ነው‌‌


We will cry today and we will laugh tomorrow
Trust us today and we will forget tomorrow
Today we are sad and tomorrow we will be happy
Nothing lasts forever
We are in this world, it will all pass…
We have a permanent country called Ahira
The main thing is to prepare for that house, my dear
That decoration is permanent‌‌
136 viewsedited  18:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-07 14:32:45
«በጨለማ ኩራዝ ለኩሼ ልብሴን እየሰፋሁ ሳለ ድንገት ኩራዙ ወደቀ'ና ክፍሉን ፅልመት ሞላው፤ መርፌዬም ወደቀች....» ስትል ትርክቷን ጀመረች ዓኢሻ (ረ.ዐ)
በዚህ ሁኔታ ሆኜ የወደቀብኝን መርፌ በዳሰሳ በመፈለግ ላይ ሳለሁ ረሱ(ሰ.ዐ.ወ) ብቅ አሉ። የክፍሉን ፅልመት የፊታቸው ኑር ገፈፈው።
ወላሂ ክፍሉ በፊታቸው ፍካት አብርቶ የጠፋብኝን መርፌ ለማግኘት አስቻለኝ።
ወደሳቸው ዞር ብዬ፦ « አባቴምእናቴም መስዋእት ይሁኑልዎ፤ ፊትዎ ምንኛ ያበራል!!!» አልኳቸው።
«ወየውላቸው የቂያማ እለት ይህን ፊቴን ለማየት
ለማይታደሉት!» አሉኝ።
«ማን ነው ይህን ፊት የቂያማ እለት የማያየው? » ስል ጠየቅኳቸው።
እሳቸውም፦ «ስሜ በሱ ዘንድ ተወስቶ ሰለዋት የማያወርድ ሰው ነው» ሲሉ መለሱልኝ።

اللهُم صلِ وسلم على نبينا مُحمد!

@elunacalligraphy
115 viewsedited  11:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-01-06 19:20:17 ታገሠኝ!
.
(#ፈይሠል_አሚን)
.
የስጋት ስንክሳር፣ከእንቅልፍ እስኪያነቃኝ፤
ሰርክ መናቸቱ፣ልግመት እስኪበቃኝ፤
ያላንተ መራመድ፣ክብደቱ እስኪገባኝ፤
እብደቱ እስኪሰማኝ፤
ታገሠኝ!
.
ከኩነኔ አድባር፣ከኃጢያታት ዋሻ፤
ጥላህ እስኪኾነኝ፣የነፍሴ ወጌሻ፤
መንገዴ እስኪወለድ፣ወዳንተ መሸሻ፤
ምሕረትን እስክሻ፤
ታገሠኝ!
.
የመቱኝ መብረቆች፣ብርሃን እስኪያውሱኝ፤
የጠፉኝ መንገዶች፣ደጅህ እስኪያደርሱኝ፤
የከሰሙት ጽንፎች፣ፍኖት እስኪኾኑኝ፤
ሸክሞች እስኪያቀኑኝ፤
ታገሠኝ!
.
ነፍሶች በተኙበት፣
በድቅድቅ አረንቋ፤
በምርኮ እስክጸድቅ፣
ለቅጽበት ቢኾን እንኳ!
ታገሠኝ!
.
አምናለሁ ጌታዬ. . .
ፈተና እና መቅሰፍት፣ ከእልፍኙ ሲመጣ፣
በብርቱ ፈልጎህ፣የለም አንተን ያጣ!
ታገሠኝ!
.
@elunacalligraphy
108 views16:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-03 07:14:18 የሩሕ ጉዞ...
(ነጃት ሀሰን)
ክፍለ - ጀማሉል ዐለም(2)

<<ሩሔ በፍቅርሁ ነዶ
ስላንቱ ሊፅፍ ወዶ
ሆነ መቃምሁ ከብዶ
ለቃሎቼ ቅጣት
ሰላም ይድረሶት ሆዴ>>

መቼስ ያን ያይኔን አበባ ችሎ የገለፀ ብዕር የለም- አወዳደስኩ ብዬ እንዳላበላሽ ጀሊሉ ይርዳኝ!
የፊታቸው ፀዳል ስንቱን በፍቅራቸው አንበረከከ!
ሰው ለሶስት ነገር ይወደዳል ይላሉ ዐዋቂዎቹ...ሶስቱም ሞልተው ፈሰውባቸዋል የኔ ዐለም! አንደኛው ጀማል ነው(ሌላው ለሌላ ቀኑ ይኖርልንና በጌትዬው እዝነትና ፈቃድ)...
ታዲያ በስል ካራ የግብፅ ወይዛዝርቱ እጃቸውን የከተፉላቸው ነብዩሏህ ዩስፍ(ዐለይሂ ሰላም) እንኳ ከኔው ዘንፋላ ውበት ተቆንጥሮ ነው የተሰጣቸው... አስባለሁ እነዛ ወይዛዝርት ሙኽታሩን ቢያዩ ምናቸውን ይቆርጡት ይሆን?(ነገሩ ቀድሞውን ሊያዩዋቸው አይቻላቸውም- የውበታቸው ፍንጥርጣሪ ለሰውኛው አይን የጠና ነውና(ወዲህም ፀሀይን መመልከት የሚያጥበረብረው ዐይን... የለይሉም የቀኑንንም ሸምስ በየትኛው ቁዋው ሊመለከት ይቻለዋል?))

<የአዒሸቱን ባል ግንባር ቢያዩማ ወይዛዝርቱ በሙላ
ልባቸውን ነበር ሚቆርጡት በጃቸው በያዙት ቢላ
መች ሚታይ ሁኖ እንደቀላል
ውበቱ ልብ ይገላል>>

የታደሉቱ የመላ አካላቸውን ውበት ሊወስፉ ብራና ወጥረው፣ ቀለም ነክረው...ለቁጥር የታከተውን ጥለውልን በናፍቆቱ እንደተወዘወዙ ወደ ወዳጃቸው ተሻግረዋል። ከፀጉራቸው የኩል ጥቁረትና ዘንፋላነት... ከሽፋሽፍታቸው ጥቅጥቅነትና ሉል አይናቸውን ዘብ መስሎ ጠባቂነት... የዛን ገዳይ አይን ንጣተ-ንጣት፣ የጥቁረቱንም ጥቁረት... የአፍንጫቸውን....የጉንጫቸውን...ፀዳለ-ውበት!
ምን ያልነኩት አለና....ወዳጃቸው ነኝ ያልን እንደሁ ሸማዒላቸውን እንገላልጠው...ሙሀባችን ይጨምርልን ዘንዳ!
ይሄ ባህር መውጫው አይታወቅም...አንተ ወዳጄ ሆይ በሰለዋት መቅዘፊያ ተሻገረው!

አሏህ ወይ የፍቅራችንን ወለል ልባችን ላይ አርጋው!
ምላሳችን ከስምህ...ወዲህም ከስማቸው አትነጥልብን!
በተወደደችው ቀን እንለምንሀለን... ሰላምን በሙእሚን ቀልብ ሁላ ላይ አስፍንልን!
አሚን!

አሏሁመ ሶሊ ወሰሊም ወባሪክ ዐላ ሰይዲና ወመውላና ሙሐመድ...ወአላ አሊሂ ወሶህቢሂ አጅመዒን!

@elunacalligraphy
154 views04:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-11-26 08:27:23 ረሱል(ﷺ) እንዲህ ብለዋል
"በጁምዓ ቀንና በጁምዓ ሌሊት
በኔ ላይ ሰለዋት ማውረድን አብዙ
በኔ ላይ አንድ ሰላዋትን ያወረደ አላህ በሱ ላይ አስር ሰላዋትን ያወርድበታል"
.
.
በይሀቂ ዘግበውታል አልባኒ ሀሰን ብለውታል
➢ረሱሉል አሚን ላይም ሰለዋት እናብዛ

للَّهُمَّ صَلِّ عَلَى مُحَمَّدٍ، وَعَلَى آلِ مُحَمَّدٍ، كَمَا صَلَّيْتَ عَلَى إِبْرَاهِيمَ، وَعَلَى آلِ إِبْرَاهِيمَ، إِنَّكَ حَمِيدٌ مَجِيدٌ، وَبَارِكْ عَلَى مُحَمَّدٍ، وَعَلَى آلِ مُحَمَّدٍ، كَمَا بَارَكْتَ عَلَى إِبْرَاهِيمَ، وَعَلَى آلِ إِبْرَاهِيمَ، فِي الْعَالَمِينَ إِنَّكَ حَمِيدٌ مَجِيدٌ

#ሰናይ_ጁምዐ

@elunacalligraphy
179 views05:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-11-23 21:25:38 ለሰው ሕልም እንቅልፍ ማጣት፣ ስለ ሰው ረሃብ መራብ፣ ለባለ ጊዜ ጊዜን መገበር፣ ዕውቀትን ተሠጥኦን፣ገንዘብን ሁሉ መሥጠት! መቼ እንደሆነ አናውቅም እንጂ አንድ ቀን ይኼ ሁሉ ይቆማል። ምክንያቱም ዓለም ተገለባባጭ ናት። ከታች ሆኖ የተረገጠ ሁሉ ከላይ ሆኖ ባይረግጥም....ግን አንድ ቀን የመረገጡን ጥዝጣዜ የጊዜ ዋግምት ያሽረዋል። ጠባሳው ባይጠፋም የመታመሙ ታሪክ ምልክት ሆኖ ህመሙ ግን ይፈወሳል።
.
የሚመጥን ኩርማን ቦታ ማጣት፣ ያለ ሥም መሠየም፣ ያለ ግብር መጠራት፣ እንደ ገለባ መቅለል፣ ማር እየተፉ በእሬት መለካት፣ እንደ ምንም..እንደ ማንም...ቢሞት የማይጎድል፣ቢኖር የማይጨምር ዓይነት ስሜት. . .መቼ እንደሆነ አላውቅም እንጂ ይኼም አንድ ቀን ከወፍ ጋር እንደ ነፈሰው ንፋስ አቅጣጫ ሳይመርጥ ይጠፋል። ምክንያቱም በጋው ይርዘም እንጂ ክረምትም የራሱ ኃይል አለው።
.
ግን እስከዚያ መዳረሻው የሚያም ዝምታ፣ የሞኝ ፈገግታ፣የሎሌ ትሕትና፣ የማያውቅ ሕፃን ዓይነት. . ."ምንም አዲስ ነገር የለም" ዓይነት ብልሃት! ዝም!
.
#ፈይሠል_አሚን

@elunacalligraphy
150 views18:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-11-19 09:18:23
ዱአችን መቅቡል የሚሆንበት፣በሰለዋት ደምቀን የምናሸበርቅበት ውብ ጁሙአ ይሁንልን!!!

اللهم صلى وسلم على نبينا محمد

elunacalligraphy||
148 views06:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-11-17 19:19:40 ·
(የሚያለቅሱበት ቂሷ)
የሰኢድ ኢብን ጁበይርን አሟሟት አስገራሚ ታሪክ ያንብቡት፡፡
``````


ሐጃጅ ሰኢድን “ ሸቂዩ ኢብኑ ከሲር ነህ አይደል ?” አለው፡፡(በአረብኛ ሸቅይ የሰኢድ ተቃራኒ ነው)
ሰኢድ፡- ስሜን ያወጣችልኝ እናቴ ጠንቅቃ ታውቀዋለች፡፡

ሐጃጀ፡-(በቁጣ) አንተም እናትህም ፉግር እድለ ቢሶች(ሸቅይ) ናችሁ፡፡
ሰኢድ፡- ሸቅይማ የጀሀነም የሆነ ሰው ነው፡፡ የሩቅ ታውቃለህ እንዴ?
ሐጃጅ፡- ዱንያህን በአንገብጋቢ ጀሀነም ነው የምቀይርልህ፡፡

ሰኢድ፡- ወላሂ ይህን ማድረግ መቻልህን ባውቅ ከአሏህ ውጭ አምላክ አድርጌ እይዝህ ነበር፡፡
ሐጃጅ፡- ለኔ ያለህ አመለካከት ምንድን ነው?
ሰኢድ፡- በሙስሊሞች ደም ተጨማልቆ አሏህን የሚገናኝ በደለኛ ነህ፡፡

ሐጃጅ፡- ይልቅ ምን አይነት አገዳደል ልግደልህ? እራስህ ምረጥ፡፡
ሰኢድ፡- አንተ ራስህ መሞቻህን መንገድ ምረጥ፡ አሏህ አኔን በገደልከኘኝ መንገድ አንተንም ይገድልሃል፡፡

ሐጃጅ፡- ካንተ በፊትም ሆነ በኋላ! የማልገድልበትን አሰቃቂ ግድያ ነው የምገድልህ፡፡

ሰኢድ፡- ስለዚህ አንተ ዱንያየን ስታበላሽብኝ በኔ ምክንያት አኺራህ ይበላሻል፡፡
ሐጃጅ የሰኢድን ብርታት ባለመቋቋሙ ወታደሮችን ጠርቶ እየጎተቱ ወስደው እንዲገድሉት አዘዘ፡፡

ሰኢድም በሐጃጅ እየሳቀበት ከገዳዮቹ ጋር ሄደ፡፡ በዚህ ጊዜ ሐጃጅ በቁጣ ሰኢድን ተጣርቶ ምንድን ነው የሚያስቅህ? አለው፡፡
ሰኢድም : እኔማ የሚያስቀኝ አንተ በአሏህ ላይ ያለህ ድፍረት እና አሏህ ባንተ ስራ ያለው ትዕግስት ነው አለው፡፡

ሐጃጅ ፦ ይህንን ሲሰማ በቁጣ ገንፍሎ ወታደሮቹን እረዱት ሲል አንቧረቀባቸው፡፡
ሰኢድም፦ ወደ ቂብላ አዙራችሁ እረዱኝ አለ፡፡ አንገቱ ላይ ሰይፍ እንዳስቀመጡበትም
“ ወጅጀህቱ ወጅሂየ ሊልለዚ ፈጦረስሰማዋቲ ወል አርዶ ሀኒፈን ሙስሊመን ወማ አነ ሚነል ሙሽሪኪን ” አለ፡፡

ይህንን የሚከታተለው ሐጃጅ ፊቱን ከቂብላ ወደ ሌላ አቅጣጫ አዙሩት አላቸው፡፡

ሰኢድም ፦ “ወሊላሂል መሽሪቁ ወል መግሪቡ ፈአይነማ ቱወልሉ ፈሰምመ ወጅሁሏህ ” የሚለውን አያህ ቀራ፡
ሐጃጅም በፊቱ ድፉት አለ፡፡

ሰኢድም “ ሚንሃ ኸለቅናኩም ወፊሃ ኑዒዱክም ወሚንሃ ኑኽሪጁኩም ታረተን ኡኽራ ” የሚለውን አያህ አነበበለት፡፡
ሐጃጅ፡- አንተ ሰኢድ ምላስህ እንዴት ለቁርአን ፈጣን ነው!!! እረዱት አለ፡፡

በዚህ ጊዜ ሰኢድ “ አሽሀዲ አንላኢላሃ ኢልለሏህ ወአንነ ሙሀመደን ረሱሉሏህ ”
ሐጃጅ ሆይ የውመል ቂያማ እስከምንገናኝ ድረስ ይህችን ንግግሬን ያዛት አለና “ አሏህ ሆይ ከኔ በኋላ ማንንም እንዳይገድል አድርገው ” ብሎ አሏህን ተማጽኖ ተገደለ፡፡

የሚገርመው ነገር ግን ከሰኢድ ሞት በኋላ ሐጃጅ በየሌሊቱ “ ምነው ይህ ሰኢድ ልተኛ ስል እግሬን እየያዘ እረፍት ነሳኝ ” እያለ እየባነነ ይጮህ ነበር፡፡
ከሰኢድ ሞት 15 ቀናት በኋላ ሐጃጅ ማንንም ሰው ሳይገድል ሞተ፡፡ አንተ የጁበይር ልጅ ሆይ አሏህ ይዘንልህ፡፡ ካንተ ፅናት፣ አሳማኝ መረጃ እና የኢማንህ ንፅህና አንፃር እኛስ የት ነን?

@elunacalligraphy
148 views16:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ