Get Mystery Box with random crypto!

ሪፖርት | ሙጂብ ቃሲም ዐፄዎቹን በዋንጫ ፉክክር አቆይቷል June 20, 2022 by socceret | @አባ ቡና ነው 🎤🎤 @ABA BUNA NEW

ሪፖርት | ሙጂብ ቃሲም ዐፄዎቹን በዋንጫ ፉክክር አቆይቷል
June 20, 2022 by soccerethiopia21
ሪፖርት | ሙጂብ ቃሲም ዐፄዎቹን በዋንጫ ፉክክር አቆይቷል
በዕለቱ የመጀመሪያ በነበረው ጨዋታ ወደ ኢትዮጵያ ከተመለሰ ወዲህ ከግብ ርቆ የሰነበተው ሙጂብ ቃሲም ያስቆጠራቸው ሁለት ግቦች ፋሲል ከነማ ከመሪው ቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር ያለውን ልዩነት አስጠብቆ እንዲቀጥል አስችሏል።
አዳማ ከተማዎች ባለፈው የጨዋታ ሳምንት በኢትዮጵያ ቡና ከተረታው ስብስብ ባደረጓቸው ለውጦች ፀጋአብ ዮሴፍ እና ቅጣት ያለበት ቶማስ ስምረቱን በዮሴፍ ዮሐንስ እና እዮብ ማቲዎስን ተክተው ያስገቡ ሲሆን በአንፃሩ ሰበታ ከተማን አሸንፈው የመጡት ፋሲል ከነማዎች ደግሞ ከድር ኩሊባሊ ፣ በዛብህ መለዮ እና ጉዳት ያገኘው ኦኪኪ አፎላቢን አስወጥተው በምትካቸው አስቻለው ታመነ ፣ ሱራፌል ዳኛቸው እና በረከት ደስታን ተክተው በማስገባት የዛሬውን ጨዋታ አድርገዋል።
እጅግ ቀዝቃዛ አጀማመር ባስመለከተን የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ በአመዛኙ አዳማ ከተማዎች ከኳስ ጀርባ በጥንቃቄ ለመከላከል ጥረት ያደረጉበት እንዲሁም ፋሲል ከተማዎች ደግሞ ይህን የአዳማን የመከላከል ውቅር ለመስበር ከፍተኛ ጥረት ሲያደርጉ የተመለከትንበት ነበር። ፋሲሎች በርከት ያሉ የኳስ ቅብብሎችን በማድረግ ወደ ተጋጣሚ ሳጥን ለመድረስ ተደጋጋሚ ጥረቶችን ያደረጉ ሲሆን በዚህም በተለይ በቀኝ መስመር በኩል የነበራቸው አፈፃፀም በንፅፅር የተሻለ ሆኖ ተመልክተናል።
በ9ኛው እና 14ኛው ደቂቃ ላይ ከቀኝ መስመር ከተሻማ ኳስ በረከት ደስታ ሁለት አጋጣሚዎችን ቢያገኝም ኳሶቹን መጠቀም ሳይችል የቀረ ሲሆን ከዚህ ውጪ በአንድ አጋጣሚ ሱራፌል ዳኛቸው ከሳጥን ውጪ ካደረገው ሙከራ ሌላ በአዳማ የሜዳ አጋማሽ እንዳሳለፉት ደቂቃ ፋሲሎች በቂ ዕድሎችን መፍጠር ሳይችሉ ቀርተዋል።