Get Mystery Box with random crypto!

የቦሌ ክ/ከተማ የሕግ ስርፀትና ምክር መስጠት ዳይሬክቶሬት

የቴሌግራም ቻናል አርማ bosub — የቦሌ ክ/ከተማ የሕግ ስርፀትና ምክር መስጠት ዳይሬክቶሬት
የቴሌግራም ቻናል አርማ bosub — የቦሌ ክ/ከተማ የሕግ ስርፀትና ምክር መስጠት ዳይሬክቶሬት
የሰርጥ አድራሻ: @bosub
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 287
የሰርጥ መግለጫ

በዚህ በቦ/ክ/ከ/ዐ/ሕ/ጽ/ቤት የሕ/ስ/ም/መ/ ዳይሬክቶሬት ቻናል ስለ ተለያዩ ሀገሮች ሕጎች(በተለይም ስለ ኢትዮጵያ ሕጎች)ማብራሪያ የሚሰጥበት፣አዳዲስ ሕጎች share የሚደረጉበት፣ወቅቱን ያገናዘቡ ዜናዎችም ሆነ መረጃዎች የሚተላለፉበት፣በዳይሬክቶሬቱ ስር የተሰጡ ግንዛቤ ማስጨበጫዎች፣የሕግ መልዕክቶች፣በራሪ ጽሑፎች እና የመሳሰሉት ወደ እናንተ ተደራሽ የሚደረጉበት ነው።
መልካም ቆይታ!

Ratings & Reviews

5.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2022-05-19 09:37:19 ሰላም ለእርስዎ ይሁን!
አንድ ሰው የወንጀል ድርጊት ፈጽሞ ከተገኘና በፍርድ ቤት ቅጣት ከተጣለበት በኋላ ቅጣቱን ሳይጨርስ ሊፈታ ነው ወይም ተፈታ ሲባል ሰምተው ያውቃሉ? ለምንና እንዴት ይህ ሊሆን እንደሚችልስ ራስዎን ጠይቀው ያውቃሉ? እንግዲያውስ መሰረቷን በተሻሻለው የኢፌደሪ የወንጀል ህግ ላይ ያደረገችውው ይህችን አጭር መልእክት በማንበብ ስለአመክሮ ያለዎትን ግንዛቤ በጥቂቱም ቢሆን ያሳድጉ!
አመክሮ፡- አንድ ተቀጪ በእስር ወቅት ባሳየው መልካም ጠባይ የተነሳ የተጣለበትን ቅጣት ሙሉ በሙሉ ሳይፈጽም አስቀድሞ ከእስር በመልቀቅ ጠባዩን ለማሻሻልና ወደ መደበኛው ማህበራዊ ኑሮ ለመመለስ ሲባል የሚሰጥ የፈተና ወይም የሙከራ ጊዜ ነው።
ማንኛውም ተቀጪ በአመክሮ ለመፈታት እጩ ሆኖ ሊቀርብ የሚችለው በቅድሚያ የሚከተሉትን ዝቅተኛ መስፈርቶች አሟልቶ ሲገኝ ነው፡-
ሀ) ከተወሰነበት የእስራት ጊዜ ከሶስት እጅ ሁለቱን እጅ ሲፈጽም፤
ለ) ፍርዱ የእድሜ ልክ እስራት ሲሆን ሀያ አመት ሲፈጽም፤
ሐ) አስፈላጊ የሆነውን ነጻነት የሚያሳጣ ቅጣት ወይም የጥንቃቄ እርምጃ በመፈጸም ላይ ሳለ በስራውና በጠባዩ የተረጋገጠ መሻሻል ካሳየ፤
መ) በፈጸመው የወንጀል ድርጊት ምክንያት ለደረሰው ጉዳት በፍርድ ቤት በተወሰነው መሰረት ወይም ከተበዳዩ ጋር በተደረገው ስምምነት መሰረት በተቻለ መጠን ሊከፍል የሚጠበቅበትን ካሳ ለመክፈሉ ማረጋገጫ ካቀረበ፤ እና
ሰ) አመሉና ጠባዩ በመልካም አኗኗር ለመኖር የሚያስችለውና በአመክሮ መፈታቱ መልካም ውጤት ሊያስገኝ ይችላል ተብሎ የሚታመንበት ሆኖ ከተገኘ።

ለየት ያለ ሁኔታ ከሌለ በስተቀር የአመክሮ ጊዜ የሚቆየው በመሰረቱ ተቀጪው ሳይፈጽመው የቀረው ቅጣት ወይም የጥንቃቄ እርምጃ እስኪፈጸም ድረስ ነው። ሆኖም አመክሮ የሚቆይበት ጊዜ በማናቸውም ሁኔታ ከሁለት አመት ሊያንስ እና ከአምስት አመት ሊበልጥ እንዲሁም ለእድሜ ልክ ጽኑ እስራት ተቀጪዎች ከአምስት አመት ሊያንስ እና ከሰባት አመት ሊበልጥ አይችልም።

ማሳሰቢያ! በኢትዮጵያ የወንጀል ህግ መሰረት ልማደኛና ደጋጋሚ ወንጀለኞች በፍጹም በአመክሮ ሊፈቱ አይችሉም!

ግንቦት 10 ቀን 2014 ኣ.ም
ፋሲካ አጌና (አቃቤ-ህግ)
175 viewsfasika aggena, 06:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-09 16:09:49 ሰላም!
መቼም ሁሉም ሰው ሻጭም ገዥም ነው ሲባል ሳይሰሙ አልቀሩም። አባባሉ እውነት አለው። ለምን ቢሉ! እዚህ መንደር ሻጭ ሆኖ የምናውቀው ሰው በሌላ ጊዜና ቦታ ገዥ ወይም ሸማች ሆኖ ይገኛልና ነው። አስረጅ አምጡ ከተባለም የሰፈርዎን ባለሱቅ ዋቢ አድርገን እናቀርባለን። እርሱ በእርስዎ ሰፈር አለ የተባለ ነጋዴ ይሁን እንጂ መርካቶ ወይም አትክልት ተራ ላለ ነጋዴ አለ የተባለ ሸማች ወይም ገዥ መሆኑን ልብ ይሏል!
እናም ከስር የሰፈሩትን የሸማቾች መብቶች ራስዎን እንደሸማችም እንደነጋዴም እያዩ እንዲያነቧቸው እንጋብዝዎታለን።
ማንኛውም ሸማች፦
1. ስለሚገዛው ዕቃ ወይም አገልግሎት ጥራትና አይነት በቂና ትክክለኛ መረጃ ወይም መግለጫ የማግኘት መብት አለው፤
2. ዕቃዎችንና አገልግሎቶችን አማርጦ የመግዛት መብት አለው፤
3. የዕቃዎችን ወይም አገልግሎቶችን ጥራት ወይም አማራጮችን በማየቱ ወይም የዋጋ ድርድር በማድረጉ ምክንያት እንዲገዛ ያለመገደድ መብት አለው፤
4. በማንኛውም ነጋዴ በትህትናና በአክብሮት የመስተናገድ እንዲሁም በነጋዴው ከሚደርስበት የስድብ፣ የዛቻ፣ የማስፈራራት እና የስም ማጥፋት ተግባር የመጠበቅ መብት አለው፤
5. በገዛው የንግድ ዕቃ ወይም አገልግሎት ላይ ያገኛቸውን ጉድለቶችና ጉድለቶቹ ሊያስከትሉ ስለሚችሉት ጉዳት ለሚመለከተው የመንግስት አካል የማሳወቅ መብት አለው፤
6. ጉድለት ያለበት የንግድ ዕቃ የተሸጠለት ወይም ጉድለት ያለበት አገልግሎት የተሰጠው ከሆነ ግዥው በተፈፀመ በ15 ቀናት ውስጥ የንግድ ዕቃው እንዲለወጥለት ወይም አገልግሎቱ በድጋሜ ያለክፍያ እንዲሰጠው ወይም የከፈለው ብር እንዲመለስለት ሻጩን የመጠየቅ መብት አለው፤
7. የንግድ ዕቃዎችን ወይም አገልግሎቶችን በመግዛቱ ወይም በመጠቀሙ ምክንያት ለደረሰበት ጉዳት የንግድ ዕቃዎቹን ወይም አገልግሎቶቹን በማቅረብ የተሳተፉ ነጋዴዎች በተናጠል ወይም በአንድነት ካሳ እንዲከፍሉት የመጠየቅ መብት አለው።

ከንግድ ውድድርና የሸማቾች ጥበቃ አዋጅ ቁጥር 813/2006 የተወሰደ
ፋሲካ አጌና (አቃቤ-ህግ)
ግንቦት 1 ቀን 2014 ኣ.ም
215 viewsfasika aggena, 13:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-06 15:32:16 ጤና ይስጥልኝ!
በኢትዮጵያ የብሔራዊ ፖሊሲ የውጭ ግንኙነት መርሆዎችን የውቃሉ?
1987 የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ-መንግስት
አንቀፅ 86
1. የኢትዮጵያን ሕዝቦች ጥቅም የሚያስጠብቅና የሀገሪቱን ሉዓላዊነት የሚያስከብር የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ ማራመድ፡፡
2. የመንግስታችን ሉዓላዊነትና እኩልነት ማክበር በሌሎች ሃገሮች ውስጥ ጣልቃ አለመግባት፡፡
3. የሀገሪቱ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ በጋራ ጥቅምና በእኩልነት ላይ የተመሠረቱ መሆኑን እንዲሁም በአለም አቀፍ ደረጃ የሚደረጉ ስምምነቶች የኢትዮጵያን ጥቅም የሚያስከብሩ መሆናቸውን ማረጋገጥ ፡፡
4. የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት የሚያስከብሩና የሕዝቦችዋን ጥቅም የማይፃረሩ ዓለም አቀፍ ሕጎችና ስምምነቶችን ማክበር፡፡
5. ከጎረቤት ሀገሮችና ከሌሎችም የአፍሪካ ሀገሮች ጋር በየጊዜው እያደገ የሚሄድ ኢኮኖሚያዊ ኅብረትና የሕዝቦች ወንድማማችነትን ማጎልበት ፡፡
6. በሀገሮች መካከል የሚነሱ ግጭቶች ሠላማዊ በሆነ መንገድ እንዲፈቱ ጥረት ማድረግ ፡፡

ቸር ይግጠመን !
አሊ ሣፊ (አቃቤ ሕግ)
ሚያዝያ 2014 ዓ.ም
207 viewsየሕግ ስርፀት እና ምክር መስጠት, edited  12:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-29 18:16:53
238 viewsfasika aggena, 15:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ