በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ በተመዘገቡ ታሪኮች ውስጥ ያለውን አሁናዊ የእግዚአብሔር መልእክት በተከታታይነት መመልከቱ መልካም ሆኖ አግኝቼዋለሁ።
ለዚህም፦
1- መጽሐፍ ቅዱስ ቢኖረን መልካም ነው።
2- ተከታታይነት ስላለው ፥ ይህንን በ "ቤተ-ዮሴፍ" ለመከታተል የሚሆን መደበኛ ጊዜ ይኑረን።
3- ድንቅ እይታችሁን እያጋራችሁ ፥ ንሥርነታችሁ ይለምልም ፤ ተሳታፊ ሁኑ።
4- የተጋራነውን ወደ ሕይዎት ለመቀየር ፥ በየጊዜው ራሳችን ቆም ብለን በመፈተሽ ተግባራዊ የሕይዎት ልምምድ እናድርግ።
5- ሌሎች ይህንን ኅብረት እንዲቀላቀሉ የድርሻችን እንወጣ
መልካም ቀን
መልካም ወር
ዮሴፍ ጌትነት