Get Mystery Box with random crypto!

ቤተ_ዜማ

የቴሌግራም ቻናል አርማ bete_zemas — ቤተ_ዜማ
የቴሌግራም ቻናል አርማ bete_zemas — ቤተ_ዜማ
የሰርጥ አድራሻ: @bete_zemas
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 233

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-05-21 19:48:01 ሰበር ዜና
++++++++++++++++++++++++++++++

"በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሆነው ዓለማዊ አጀንዳ ቢያራምዱም በከፍተኛ ትዕግስት ስናልፋቸው የነበሩ አባቶች ዛሬም ቤተክርስቲያን ውስጥ ሆነው ቤተክርስቲያንን ሲገፉ በዝምታ የምናይበት ሂደት አይኖርም፡፡"
++++++++++++++++++++++++++++++

ወቅታዊ የቤተ ክርስቲያን ችግርን ለመቅረፍ  በቋሚ ሲኖዶስ የተቋቋመው ዐብይ ኮሚቴ በኤጲስ ቆጶሳት ሹመት ሂደት ላይ መግለጫ አወጣ።

በአለፉት ሁለት ሦስት ቀናት በአባቶች ዘንድ ውይይት ተደርጎበት ስምምነት ላይ ሳይደረስበት የቀረው የኤጲስ ቆጶሳት ሹመት ሂደትን አስመልክቶ በተደረገው  ውይይት ላይ በአባቶች የተፈጠረው  የሐሳብ መከፋፈልና አለመግባባት ሁኔታ ካለው ተጨባጭ ሁኔታ አንጻር ለኮሚቴው በእጅጉ እያሳሰበው ይገኛል ሲል ከ10 በላይ ማኅበራትን የወከለው ኮሚቴው በመግለጫው ጠቅሷል።

በየጊዜው በሚነሱ ወሳኝ የቅድስት ቤተክርስቲያን አጀንዳዎች ውስጥ ለቅድስት ቤተክርስቲያን ጀርባቸውን የሚሰጡ፣ በቅድስት ቤተክርስቲያን ውስጥ ሆነው ዓለማዊ አጀንዳ የሚያራምዱና ከዛሬ ነገ የቤተክርስቲያንን ፍቅርና ምህረት ተረድተው ወደልባቸው ይመለሳሉ በማለት በከፍተኛ ትዕግስት ስናልፋቸው የነበሩ አባቶች ዛሬም ቤተክርስቲያን ውስጥ ሆነው ቤተክርስቲያንን ሲገፉ በዝምታ የምናይበት ሂደት አይኖርም ያለው ኮሚቴው
በዚህ ታሪካዊ ወቅት ለቅድስት ቤተክርስቲያን መቆም ሲገባችሁ እየሰማችሁ እንዳልሰማችሁ ሆናችሁ በዝምታ የምትመለከቱ አባቶችም ሆነ ዋነኛ የችግሩ አካላት የሆናችሁ አባቶች በእግዚአብሔርም በታሪክም በእኛም በልጆቻችሁ የሚያስጠይቃችሁ መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን ሲል አፅንዖት ሰጥቷል።

ቤተክርስቲያን ከማይጠፋ ዘር በክርስቶስ ደም የተመሠረተች እንጂ እንደ ፖለቲካ ምክር ቤት በዘር በጎሣ የተመሠረተች አይደለችም። ቤተክርስቲያን የሁሉም ለሁሉም ነች ያለው ዐብይ ኮሚቴው ዛሬ በወከባና በጫና ለተለየ ብሔርና ጎሣ ተለይቶ የኢጲስ ቆጶስ ሲመት ቢሰጥ ነገ በዚህ ሰበብ ቤተክርስቲያንን ለመከፋፈል ዘርና ቋንቋን መሠረት አድርጎ የሚከተለውን ጥያቄና በጥንታዊት  ሐዋርያዊት ዓለም አቀፋዊት አንዲት ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ላይ የተነጣጠረውን የፈተና እና የመከራ ማእበል መመለስም መዳኘትም ይከብዳል ብሏል።

ይህን ጽንፍ የወጣ አጀንዳ በድምጽ ብልጫ በማስወሰን ሕገ ቤተ ክርስቲያንን እና ቀኖናን በመጣስ መፍትሔ የሚያመጡ መስሎአቸው የሚተጉ አባቶችም ቤተክርስቲያንን ወደማትወጣው መከራና ፈተና እየገፏት እንደሆነ ሊረዱት ይገባል ብለን እናምናለን።

በዚህ መግለጫ ብፀዓን አባቶችንን በታላቅ ትህትና ዐቢይ ኮሚቴው ማሳሰብ የሚፈልገው ይህ አጀንዳ አስተዳደራዊ ሳይሆን ሃይማኖታዊ/ዶግማዊ እና ሥርዓታዊ/ቀኖናዊ አጀንዳ በመሆኑ በሕገ ቅድስት ቤተክርስቲያን አንቀፅ 19፡ 5፡ ሐ መሰረት በሙሉ ድምጽ እንጂ በድምፅ ብልጫ ስምምነት ተደርጎበት ውሳኔ ላይ ሊደረስ የማይገባው አጀንዳ መሆኑንም ኮሚቴው በሚገባ ያምናል ብሏል፡፡

በተለይም ይህ አለመግባባት እየሰፋ መጥቶ ውሳኔው በድምጽ ብልጫ የሚደረግ ከሆነ ሕገ ቤተክርስቲያንን እና ቀኖና ጥሰትን ስለሚያመጣ፤ ውጤቱም በብፁዓን አባቶች መካከል ያለውን መከፋፈል አስፍቶ ቤተክርስቲያንን ወደ ከባድ ፈተና የሚያደርስ ጉዳይ በመሆኑ ብፁዓን አባቶች በፍፁም መከባበር፤ ምድራዊ እና በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ዘንድ ፍጹም ጸያፍ እና የተወገዙ በሆኑ ጉዳዮች፣ዘርን፣ ቋንቋን፣ ጎጥን ፖለቲካን፣የግል ጥቅምንና ፍላጎትን ሳይሆን የረቂቃኑ እና ግዙፋኑ፤ የሰማያውያን እና የምድራውያን ልዩ ጉባኤ፤አንዲት የክርስቶስ አካል የሆነችውን ቅድስት ቤተክርስቲያንን ማዕከል በማድረግ ብቻ አንድ ልብ አንድ ሐሳብ ሆናችሁ በእርጋታ በመነጋገር ለቅድስት ቤተክርስቲያን የሚጠቅም ውሳኔ በአንድ ድምፅ ሰጥታችሁ እንደምትወጡና የአሁኑንም ሆነ የሚመጣውንም ትውልድ የመከራ ቀንበር እንደምታቀሉ ባለሙሉ ተስፋ ነን፡፡

መግለጫው ከቅዱስ ሲኖዶስ የምንጠብቀው ውጤት በማለት ዐራት ነጥቦችን ዘርዝሯል።

0ቢይ ኮሚቴው በጥር 14 ቀን 2015 ዓ.ም. ከተከናወነው  ሕገ ወጥ የኤጲስ ቆጶሳት ሢመት ጋር በተያያዘ በቤተ ክርስቲያን ላይ የተጋረጠው አደጋ መነሻ አድርጎ የተቋቋመ ሲሆን ከ10 በላይ ማኅበራትን ማለትም ከሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት፣ ከነገረ መለኮት ምሩቃን ማኅበር፣ የሀገር ሽማግሌዎች እና የምዕመናን ኅብረት፣ ማኅበረ ቅዱሳን፣ ጴጥሮሳውያን ኀብረት፣ የጎልማሶች እና ወጣቶች ማኅበር፣ ከወልዳ ዳንዲ አቦቲ፣ ከደጆችሽ አይዘጉ ማኅበር፣ ከሕግ ባለሙያዎች እንዲሁም ከጠቅላይ ቤተ ክህነት የተለያዩ መምሪያዎች የተወጣጣ ነው፡፡
21 views16:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-20 16:24:46 ድንግልም በሆድዋ ውስጥ የልጅዋ መልክ በሚለዋወጥ ጊዜ ከእርሱ ጋራ መልኳ ይለዋወጥ ነበር። እንደ ሮማን አበባ የምትቀላበት ጊዜ አለ እንደናርዶስም የምታብለጨልጭበት ጊዜ አለ የለመለመ ቅጠል የምትመስልበትም ጊዜ አለ ከወለደች በኋላ ግን አልተለወጠችምና ዮሴፍ በአንድ በቀድሞው ኅብረ መልኳ ተወስናለት መልኳን ተረዳ ማለት ነው አለው። በዚያን ጊዜ በንጉሥ አዳራሽ ውስጥ ከወርቅ የተሠራ የእመቤታችን አምላክን የወለደች የድንግል ማርያም ሥዕል ነበረችና አፈ ወርቅ ዮሐንስ ልሳነ ወርቅ ዮሐንስ አፈ በረከት ዮሐንስ መልካም ተናገርክ የሚል ቃል ከእርሷ ወጣ።

ንጉሡና ከእርሱ ጋር ያሉት በሰሙ ጊዜ እጅግ አደነቁ እግዚአብሔርንም አመሰገኑት በዚያን ጊዜ ንጉሥ አዝዞ ወርቅ ሠሪ አስመጥቶ ለከበረ ዮሐንስ የወርቅ ልሳን አሠርቶ ለሚያየው ሁሉ መታሰቢያ ምልክት ሊሆን አምላክን ከወለደች ከእመቤታችን ከድንግል ማርያም ሥዕል ዘንድ ሰቀለው። ቅዱስ ዮሐንስንም ከዚያች ቀን ወዲህ ልሳነ ወርቅ ብሎ ጠራው አፈ ወርቅም ተብሎ እስከዛሬ ተጠራ።

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሱ ጸሎትና ምልጃ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
34 views13:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-20 16:24:46 #ግንቦት_12

#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ

በዚህችም ዕለት የዓለሙ ሁሉ መምህር የሆነ የከበረ አባት ዮሐንስ አፈወርቅ አረፈ፡፡ ይህም አባት ከእስክንድርያ አገር ሰዎች ወገን ነው የአባቱም ስም አስፋኒዶስ የእናቱም ስም አትናሲያ ነው እሊህም እጅግ ባለጸጎች ነበሩ ይህንንም ልጃቸውን በመልካም አስተዳደግ አሳደጉት ትምህርትንና ጥበብንም ሁሉ አስተማሩት እርሱ ወደ አቴና ሒዶ በመምህራን ቤት ተቀምጦ ትምህርትን ሁሉ ተምሮ በዕውቀቱ ከብዙዎች በላይ ከፍ ከፍ ብሏልና።

ከዚህም በኋላ ገና በታናሽነቱ መነኰሰ የዚህንም የኃላፊውን ዓለም ጣዕም ንቆ ተወ ከእርሱም ቀድሞ በዚሁ ገዳም ቅዱስ ባስልዮስ መንኵሶ ነበር በአንድነትም ተስማምተው ብዙ ትሩፋትን ሠሩ ወላጆቹም በሞቱ ጊዜ ከተውለት ገንዘብ ምንም ምን አልወሰደም ለድኆችና ለምስኪኖች ሰጠ እንጂ ከዚያም በምንኵስና ሥራ በመጠመድ ፍጹም ገድልን እየተጋደለ ኖረ።

በዚያም ገዳም ሶርያዊ ጻድቅ ሰው ስሙ ሲሲኮስ የሚባል መነኰስ ነበረ እርሱም ወደፊት የሚሆነውን በመንፈስ ቅዱስ ያይ ነበር በአንዲት ሌሊትም ለጸሎት እየተጋ ሳለ ሐዋርያትን ጴጥሮስንና ዮሐንስን አያቸው ወደ ዮሐንስ አፈወርቅ ገብተው ጴጥሮስ መክፈቻ ሰጠው ወንጌላዊ ዮሐንስም ወንጌልን ሰጠው እንዲህም አሉት በምድር ያሠርከው በሰማይ የታሠረ ይሆናል በምድርም የፈታኸው ደግሞ በሰማያት የተፈታ ይሆናልና በውስጥህ መንፈስ ቅዱስ ያደረብህ አዲስ ዳንኤል ሆይ የክብር ባለቤት ከሆነ ከታለቅ መምህር ኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ ወደ አንተ ተልከናልና ዕወቅ እኔም የመንግሥተ ሰማያት መክፈቻ የተሰጠኝ ጴጥሮስ ነኝ። ሁለተኛውም እኔም በመጀመሪያው ስብከቴ በከበረ ወንጌል ቃል አስቀድሞ ነበረ ያልኩ ይህም ቃል በጠላት ላይ የእሳት ሰይፍ የሆነ ዮሐንስ ነኝ። ለአንተም ከክብር ባለቤት ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘንድ ወገኖችህ ምእመናንን በቀናች ሃይማኖት ታሳድጋቸው ዘንድ ዕውነተኛ አእምሮ ደግሞ ተሰጥቶሃል። ጻድቅ ሲሲኮስም ይህን ራእይ በአየ ጊዜ ቅዱስ ዮሐንስ ቸር ታማኝ እረኛ ሁኖ እንደሚሾም ዐወቀ። ከዚህም በኋላ በቅዱስ ዮሐንስ ላይ የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ በላዩ ወርዶ አደረበትና ብዙ ድርሳናትንና ተግሣጻትን ደረሰ ዲያቆን ሁኖ ሳለም የቤተ ክርስቲያንን መጻሕፍት ብሉያትንና ሐዲሳትን ተረጐመ።

በአንዲት ሌሊትም ቅዱስ ዮሐንስ ሲጸልይ የእግዚአብሔር መልአክ በድንገት እንደ በረድ ነጭ በሆነ ልብስ ተገለጠለት ቅዱስ ዮሐንስም ሲያየው ደንግጦ በምድር ላይ ወደቀ መልአኩም አርአያውን ለውጦ እንደ ሰው ሁኖ ታየው ወዳጄ አዲስ ዳንኤል ሆይ አትፍራ ተነሣ አለው የቅዱስ ዮሐንስም ልቡ ተጽናንቶ ጌታዬ አንተ ማነህ ግርማህ አስፈርቶኛልና አለው የእግዚአብሔር መልአክም ትሠራው ዘንድ የሚገባህን ልነግርህ ወዳንተ የተላክሁ ነኝ። አሁንም እግዚአብሔር አምላክ ያዘዘህን ለመሥራት ልብህን አበርታ ቃልህ ከጽንፍ እስከ ጽንፍ በአራቱ ማእዘን ይደርሳልና እልፍ አእላፋትም ትምህርትህን ተቀብለው ትእዛዝህን ሰምተው ወደ ፈጣሪያቸው እግዚአብሔር ተመልሰው ይድናሉና በእግዚአብሔር መንግሥትም ውስጥ የጸና የብርሃን ዐምድ ትሆናለህና። እነሆ የአንጾኪያ ሊቀ ጳጳሳት ወደ አንተ ይመጣል ከእርሱም ጋራ ሁሉም ካህናትና ዲያቆናት በየማዕረጋቸው የሚያዝህንም አድርግ የእግዚአብሐር ትእዛዝ ነውና ልትተላለፍ አይገባህም አለው።

ከዚህም በኋላ ያ መልአክ ለአባ ፊላትያኖስ ተገልጦ ቅዱስ ዮሐንስን ቅስና እንዲሾመው አዘዘው በማግሥቱም ሊቀ ጳጳሳቱ መጣ ከርሱ ጋራም ካህናት አሉ ይህን ቅዱስ ዮሐንስንም ይዞ ቅስና ሾመው። የቍስጥንጥንያ ሊቀ ጳጳሳትም በአረፈ ጊዜ ንጉሥ አርቃድዮስ ልኮ አስመጥቶ ቅዱስ ዮሐንስን በቍስጥንጥንያ ላይ ሊቀ ጵጵስና ሾመው አባቶቻችን ሐዋርያት እንደሚአደርጉት በሊቀ ጵጵስናው ሥራ ላይ ጸና ሕይወትነት በአላቸው ትምህርቶችና ተግሣጾች ሕዝቡን ሁልጊዜ የሚአስተምር ሆነ። ከኤጲስቆጶሳትም ሆነ ከመንግሥት ወገን ሕግን የሚተላለፉትን ሁሉ ይገሥጻቸዋል ማንንም አይፈራም ፊት አይቶም አያደላም።

የንጉሥ አርቃድዮስ ሚስት አውዶክስያም ገንዘብ ወዳጅ ስለሆነች የአንዲት ድኃ መበለት ቦታዋን በግፍ ወሰደች ያቺ መበለትም ወደ ቅዱስ ዮሐንስ መጥታ ንግሥት አውዶክስያ ቦታዋን እንደነጠቀቻት ነገረችው እርሱም የደኃዋን ቦታዋን መልሺላት ብሎ ከብዙ ምክር ጋር እንድትመልስላት ንግሥት አውዶክስያን ለመናት እርሷ ግን እምቢ በማለት አልታዘዘችለትም ወደ ቤተ ክርስቲያን ገብታ ሥጋውን ደሙን እንዳትቀበል አውግዞ ለያት።

ቍጣንና ብስጭትንም ተመልታ ስለ ክፉ ሥራቸው ከሹመታቸው እርሱ የሻራቸውን ኤጲስቆጶሳት ሰበሰበች እነርሱም ንግሥቲቱን ስለ ተቃወመ ስደት እንደሚገባው በእርሱ ላይ ተስማምተው ጻፉ እርሷም አጥራክያ ወደ ሚባል ደሴት ሰደደችው። ከዚያም በደረሰ ጊዜ የዚያች ደሴት ሰዎች በክፉ ሥራ ጸንተው የሚኖሩ ከሀድያን ሁነው አገኛቸው ቅዱስ ዮሐንስም አስተማራቸው ገሠጻቸውም በፊታቸው ስለ አደረጋቸው ድንቆች ተአምራት ወደ ቀናች ሃይማኖት አስገባቸው።

የሮሜ ንጉሥ አኖሬዎስና ሊቀ ጳጳሳቱ ዮናክኒዶስ ስለ ቅዱስ ዮሐንስ ስደት በሰሙ ጊዜ እጅግ አዘኑ በንጉሥ አርቃድዮስ ላይም በመቆጣት እንዲህ የሚል ደብዳቤ ጽፈው ላኩ ከዚህ ከክፉ ሥራ ተጠበቅ ትእዛዛችንንም ተቀብለህ የከበረ ዮሐንስን ከስደቱ ከአልመለስከው በአንተና በእኛ መካከል ሰላም አይኖርም።

መልእክታቸውንም በአነበበ ጊዜ እጅግ አዘነ ሚስቱንም አግዶ ልኮ ቅዱስ ዮሐንስን ከስደቱ መለሰው በተመለሰ ጊዜም የቍስጥንጥንያ ሰዎች በመመለሱ ታላቅ ደስታ አደረጉ። ከጥቂት ቀኖች በኋላም ንግሥቲቱ ወደ ክፋቷ ተመልሳ ሁለተኛ ወደ አጥራክያ ደሴት ሰደደችውና በዚያው አረፈ።

ንጉሥ አኖሬዎስና ሊቀ ጳጳሳት ዮናክኒዶስም በሰሙ ጊዜ መልእክትን ላኩ ሊቀ ጳጳሳቱም የከበረ ዮሐንስን ከስደቱ እስከምትመልሰው ድረስ ሥጋውንና ደሙን እንዳትቀበል አውዶክስያን አወገዛት።

ከዚህም በኋላ የከበረ ዮሐንስን ይመልሱት ዘንድ ንጉሥ ላከ ግን ሙቶ አገኙት ሥጋውንም ተሸክመው ወደ ቊስጥንጥንያ ከተማ አደረሱት። የከበረ ዮሐንስም በተሰደደበት አገር እንደአረፈና ሥጋውንም ወደ ቍስጥንጥንያ ከተማ እንደአመጡ ወደ አባ ዮናክኒዶስ መልእክት ጽፈው አስረዱት። ሁለተኛም የሮሜ ሊቀ ጳጳሳት ወደ ቤተ ክርስቲያን ገብታ ሥጋውንና ደሙን እንዳትቀበል ልኮ አውድክስያን አወገዛት እየለመነችውም ስምንት ወር ያህል ኖረች በብዙ ልመናም ፈታት። ነገር ግን ጭንቅ በሆነ ደዌ እግዚአብሔር አሠቃያት ያድኗት ዘንድ ገንዘቧን ለባለ መድኃኒቶች ጥበበኞች እስከ ሰጠች ድረስ ግን አልዳነችም ወደ ቅዱስ ዮሐንስ መቃብርም ሔዳ በእርሱ ላይ ያደረገችውን በደል ይቅር ይላት ዘንድ እየሰገደችና እያለቀሰች ለመነችው እርሱም ይቅር አላት ከደዌዋም ፈወሳት። ጌታችንም ከሥጋው ታላላቅ ድንቆች ታአምራትን ገለጠ።
የከበረ ዮሐንስም ንጉሥ ሆይ እንዲህ አትበል እንዲህ አንተ እንደምትለው አይደለም የከበረች ድንግል እመቤታችንስ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሆድዋ ውስጥ በነበረ ጊዜ የእርሱ ኅብረ መልክ በሚለዋወጥ ጊዜ ከእርሱ ጋር መልኳ ይለወዋወጥ ነበር። በንጹሕ ብርሌ ውስጥ ውኃ በጨመሩ ጊዜ ውኃ መስሎ እንደሚታይ ወይን ጠጅም ቢጨምሩ ያንኑ መስሎ እንደሚታይ ወይም ከውስጡ በተጨመረው ቀይም ቢሆን ቀልቶ እንደሚታይ ቅጠልያም ቢገባበት ቅጠልያ መስሎ እንደሚታይ።
31 views13:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-19 20:43:39
ግንቦት 12 ተክለሃይማኖት ወክርስቶሰ ሰምራ ሥርዓተ ማኅሌት
 
ስምዓኒ እግዚኦ ጸሎትየ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ   ወይብጻሕ ቅድሜከ ገአርየ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ወኢትሚጥ ገጸከ እምኔየ በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ እዝነከ ኀቤየ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ  አመ ዕለተ እጼውአከ ፍጡነ ስምዓኒ  ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ለዓለም ወለዓለመ ዓለም ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል ንወድሶ ለዘሃሎ እግዚአብሔር ልዑል ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ በአሐቲ ቃል

ነግሥ
ሰላም ለአብ ገባሬ ኲሉ ዓለም ለወልድ ሰላም ወለመንፈስ ቅዱስ ሰላም ለማርያም ሰላም ወለመላእክት ሰላም ሰላም ለነቢያት ወለሐዋርያት ሰላም ለሰማእታት ሰላም ወለጻድቃን ሰላም

ዚቅ
ሰላም ለክሙ ኦ ማኅበራኒሁ ለክርስቶስ  እለ ተጋባዕክሙ ውስተ ዝንቱ ቤት  ጳጳሳት ቀሳውስት ወዲያቆናት ሰላም ለክሙ ማኅበረ ደናግል ወመነኮሳት  እለ ተመሰልክሙ ከመ መላእክት

መልክዐ ሚካኤል
ሰላም ለሕፅንከ እንተ በዲቤሁ ሕቁፍ  ጸሎተ ቅዱሳን ውኩፍ  ሚካኤል ክቡር መስፍነ ትጉሃን አዕላፍ ለረዲኦትየ ከመ ዘይሠርር ዖፍ  እንዘ ትሠርር ነዓ በክልኤ አክናፍ

ዚቅ
ወሚካኤል አሐዱ እመላእክት  እምቅዱሳን ቀደምት እስመ በዲበ ሠናይቱ ለሰብእ ተአዛዚ

ወረብ
ሚካኤል መልአክ አሐዱ አሐዱ እመላእክት
እስመ በዲበ ሠናይቱ ለሰብእ ተአዛዚ

ነግሥ
ሰላም ለገቦከ በአክናፈ ብርሃን ግልቡብ: እንተ በዲቤሁ ይጼልል መንፈሰ ኪሩብ: ሚካኤል መልአኩ ለእግዚአብሔር አብ: አጥረየ በረድኤትከ መዓርገ ስብሐት ዕፁብ  :ተክለሃይማኖት የዋህ ወብእሲ ጠቢብ

ዚቅ
ተክለሃይማኖትኒ ይቤ ነዋ ሚካኤል አሐዱ እመላእክት  እምቅዱሳን ቀደምት መጽአ ይርድዓኒ አጽንዓኒ ወይቤለኒ ኢትፍራህ ብእሴ ፍትወት አንተ ሰላም ለከ ጽናዕ ወተአገሥ  ወእንዘ ይትናገረኒ ጸናዕኩ  ወእቤሎ ንግረኒ እስመ አጽናዕከኒ  ወይቤለኒ ሶበ ተአምር ዳዕሙ ሚካኤል መልአክክሙ

ወረብ
ይቤ ነዋ ሚካኤል አሐዱ እመላእክት እምቅዱሳን ቀደምት እምቅዱሳን
መጽአ ይርድዓኒ ይቤ ተክለሃይማኖት

መልክዐ ተክለሃይማኖት
ሰላም ለዝክረ ስምከ ዘጥንተ ፊደሉ መስቀል  ስም ክቡር ወስም ልዑል ተክለሃይማኖት ማቴዎስ በዓለ ቀዳማይ ወንጌል ከመ እወድሰከ መጠነ አውሥኦተ እክል ማዕሠረ ልሳንየ ትፍታሕ ማርያም ድንግል

ዚቅ
ናሁ ዝክርከኒ ኢይጠፍዕ  ወመንፈስከኒ የዓቅቡ መላእክት በሰማያት ኢይትኃጎል ሥጋከ በዲበ ምድር ብጹዕ ብእሲ ዘይፈርሆ ለእግዚአብሔር

ወረብ
ናሁ ዝክርከኒ ኢይጠፍዕ ወመንፈስከኒ የዓቅቡ መላእክት
ኢይትኃጎል ሥጋከ ሥጋከ ተክለሃይማኖት

መልክዐ ተክለሃይማኖት
ሰላም ለልብከ ቅዱስ ወቡሩክ ዘዐቀበ ሕጎ ለወልደ ማርያም አምላክ  ተክለሃይማኖት አሐዱ እምዐሳባውያን ዘሠርክ እምይእቲ ዐስበ ፃማከ ዘኢትትኃደግ በበክ  ያስተሣትፈኒ ለፅሩዕ ሚካኤል መልአከ

ዚቅ
መላእክት ወሰብእ አሐዱ ማኅበሮሙ በእንተ መስቀሉ ለክርስቶስ አለደ መርዔተ ኮኑ

ወረብ
አሐዱ ማኅበሮሙ ክርስቶስ ሠምራ ወተክለሃይማኖት
በእንተ መስቀሉ ለክርስቶስ አሐደ መርዔተ ኮኑ

መልክዐ ተክለሃይማኖት
ሰላም ለፍልሰተ ሥጋከ እምውሳጤ ገዳም ዔላመ ወእምነ ዔላምኒ ደብረ ሊባኖስ ዳግመ ተክለሃይማኖት ባህለ ከመ ወንጌላዊ ቀደመ  እመ ረከቡ ደቂቅከ በዓለም ሕማመ  በኀቤከ አባ ይርከቡ ሰላመ

ዚቅ
ትዌድሶ ደብረ ሊባኖስ ገዳሙ  ለተክለሃይማኖት ጻድቅ መጠነ በዝኃ ሕማሙ  ትዌድሶ ደብረ ሊባኖስ ገዳሙ  እስመ በውስቴታ ተገብረ ፍልሰተ ሥጋሁ ወዓፅሙ  ትዌድሶ ደብረ ሊባኖስ ገዳሙ እምነ አድባራት ኲሎን ዘተለዓለት በስሙ  ትዌድሶ ደብረ ሊባኖስ ገዳሙ ኢየሱስ ክርስቶስ እንተ ቀደሳ በደሙ ትዌድሶ ደብረ ሊባኖስ ገዳሙ ትዌድሶ ደብረ ሊባኖስ ገዳሙ።

ዓዲ ዚቅ
ተክለሃይማኖት ድንግል ወንጹሕ ይጸርሕ እንዘ ይብል  እስመ አብርሃት ለዛቲ መካን ፈድፋደ እምኮከበ ጽባሕ።

ምልጣን
አባ አቡነ አቡነ መምህርነ እምአዕላፍ ህሩይ ሐውጽ እምሰማይ ብርሃነከ ከመ ንርዓይ አማን ተክለሃይማኖት ፀሐይ።

አመላለስ
አማን በአማን
ተክለሃይማኖት ፀሐይ

ቅንዋት፦
ነዓምን ከመ ሞተ ወተንሥአ....

https://t.me/bete_zemas
https://t.me/bete_zemas
https://t.me/bete_zemas
27 views17:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-19 14:24:22 ቀጥሎም የዙር አባን ቤተ ክርስቲያን ለማሠራት ወደ ጋይንት በተጓዙ ጊዜም በዚያ ሁለት ዓመት ዝማሬ መዋሥዕት የተባለ ድርሰቱን አስተምሯል፡፡ ይህ ቦታ እስከ ዛሬ የዚህ ትምህርት ማስመስከሪያ ነው፡፡
ቅዱስ ያሬድ ከዚያ በኋላ ወደ አከሱም ተመልሶ በመደባይ ታብር በተባለ ቦታ ቅዳሴያትን በዜማ አዘጋጅቷል፡፡ ይህ ቦታ ከአከሱም 15 ኪ.ሜ ርቆ ይገኛል፡፡ ከዚህ በኋላ ለመጨረሻ ጊዜ አክሱምን ተሰናብቶ ለመሄድ ወደ ጽዮን ቤተ ክርስቲያን ገባና «ቅድስት ወብጽዕት ስብሕት ወቡርክት ክብርት ወልዕልት አንቀጸ ብርሃን ማዕርገ ሕይወት» እያለ አንቀጸ ብርሃን የተባለውን ድርሰቱን ሰተት አድርጎ አዘጋጀው፡፡

ይህንን ድርሰት ሲያዜም አንድ ክንድ ያህል ከምድር ከፍ ብሎ ይታይ ነበር ይባላል፡፡ ቅዱስ ያሬድ በሰሜንና ወገራ፣ አገውና በጌምድር እየተዘዋወረ አስተምሮ ከሰሜን ተራራዎች ውስጥ እየጾመና እየጸለየ በብሕትውና ለብዙ ዘመን ከኖረ በኋላ በሰሜናዊ ምሥራቅ በኩል ባለው በጸለምት ዋሻ ውስጥ በ571 ዓ.ም ግንቦት 11 ቀን ተሠውሯል፡፡

ይህ ቦታ በተለምዶ የሰሜን ተራሮች በሚባለው ወስጥ የሚገኝ ከፍተኛና ብርዳማ ቦታ ነው፡፡

ቅዱስ ያሬድ ለኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ሰማያዊ ዜማን ከማበርከቱም ሌላ በትምህርት ሂደትም አስተዋጽዖ አድርጓል፡፡ የድጓን፣ የጾመ ድጓን የዝማሬ መዋሥዕትንና የቅዳሴን ትምህርት ከማስተማሩም በላይ ለቅኔ ትምህርትም መሠረት ጥሏል፡፡ ቅዱስ ያሬድ በዓለም የመጀመርው የዜማ ኖታ/ ምልክት/ ባለቤት ነው።

በእውነት የቅዱስ ያሬድን ጸጋ ያብዛልን ረድኤቱ ፣ በረከቱ ፣ ቃል ኪዳኑን ያብዛልን አሜን አሜን።
https://t.me/bete_zemas
https://t.me/bete_zemas
https://t.me/bete_zemas
32 views11:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-19 14:24:22 ​​እንኳን ለቅዱስ ቅዱስ ያሬድ ዓመታዊ ክብረ በዓል አደረሰን አደረሳችሁ።

#ቅዱስ_ያሬድ_ማነው?

የቅዳስ ያሬድ አባቱ አብድዩ / ይስሐቅ/ እናቱ ክርስቲና /ታውክልያ / ይባላሉ። በሌላም በኩል አባቱ እንበረም እናቱ ትውልያ ይባላሉ የሚል ታሪክም አለ፡፡ የትውልድ ሥፍራው አክሱም ነው፡፡

የተወለደው በ505 ዓ.ም/ ሚያዝያ 5 ቀን ሲሆን በተወለደ በ7 ዓመቱ ወላጅ አባቱ ስለሞተ እናቱ የአክሱም ጽዮን መምህር ለነበረው ለአጎቱ ለጌዴዎን እያስተማረ እንዲያሳድገው ሰጠችው፡፡ ከአባ ጌዴዎንም ዘንድ እየተማረ ለ25 ዓመት ተቀመጠ፡፡

ሆኖም ቃለ እግዚአብሔር የመቀበል ችሎታው ደካማ ስለሆነ በጣም ያዝን ነበር፡፡ ከዕለታት አንድ ቀን ከትምህርት ድክመቱ የተነሣ አጎቱ በጨንገር ቢገርፈው በዚህ ተበሳጭቶ ትምህርቱን ትቶ ሄደ፡፡ በመንገድም ሲጓዝ ውሎ በቀትር ደክሞት ከዛፍ ሥር ዐረፈ፡፡

በዚያ ጊዜ አንድ ትል ከዛፉ ላይ ያለውን ፍሬ ለመብላት ስድስት ጊዜ በመውደቅና በመነሣት ዛፉ ላይ ለመውጣት ሞክሮ በሰባተኛው ሰተት ብሎ ወጥቶ ሲበላ ተመለከተ፡፡ እርሱም በፈጸመው የብስጭት ተግባር በመጸጸት ተመልሶና አጎቱን ይቅርታ ጠይቆ ትምህርቱን ቀጠለ፡፡

አጎቱም ተደስቶ ዓይነ ልቡናውን ያበራለት ዘንድ እያለቀሰ ፈጣሪውን ለመነለት፡፡ እግዚአብሔርም ጸሎቱን ሰምቶ ለቅዱስ ያሬድ ዕውቀትን ገልጾለት መጻሕፍተ ብሉያትንና ሐዲሳትን ዐወቀ፡፡

ከዚያም በኋላ ወደ መምህሩ ተመልሶ ትምህርቱን ቀጠለና ቅዱሳት መጻሕፍትን በሚገባ አጠና፡፡ ሢመተ ዲቁናን ቀጥሎም ሢመተ ቅስናን ተቀበለ፡፡ ቅዱስ ያሬድ ግእዝ፣ እዝልና አራራይን ከሦስት ወፎች/መላእክት በወፎች ተመስለው/ መማሩን ሊቃውንት ይገልጣሉ፡፡

እነዚህ በወፍ የተመሰሉ መላእክት እየመሩት ወደ አርአያም አርጎ የ24ቱን ካህናተ ሰማይ ዜማ ከተማረ በኋላ ጠዋት በ3 ሰዓት በአክሱም ቤተ ክርስቲያን «ሃሌ ሉያ ለአብ ሃሌ ሉያ ለወልድ ሃሌ ሉያ ለመንፈስ ቅዱስ ቀዳሚሃ ለጽዮን ሣረረ ወበዳግመ አረአዮ ለሙሴ ዘከመ ይግበር ግብራ ለደብተራ» ብሎ አዜመ፡፡

ይህን ዜማ የደረሰበት ወሩ ታኅሳስ ቀኑም ዕለተ ሰኞ ነው ይባላል፡፡ የቅዱስ ያሬድ የመጀመሪያ ዜማው «አርያም» በመባል ይታወቃል፡፡ ይህም ከመላእክት ወይም ከሰማይ የተገኘ መሆኑን ለማጠየቅ የተሰጠው ስም ነው፡፡

ቅዱስ ያሬድ ይህንን ዜማ በተመስጦ ሲያዜም ንጉሡ ፣ ንግሥቲቱ ፣ ጳጳሱ መኳንንቱና ካህናቱ ወደ አኩስም ቤተ ክርስቲያን ተሰባስበው መጥተው በአድናቆት ያዳምጡት ነበር፡፡ ምክንያቱም ገድለ ቅዱስ ያሬድ እንደሚገልጥልን ከዚያ በፊት በውርድ ንባብ ከሚደረግ ጸሎትና መንፈሳዊ አገልገሎት በቀር ይህን የመሰለ ዜማ አልነበረምና፡፡

የቅዱስ ያሬድ ድርሰት ብሉይን ከሐዲስ ያስማማ ፣ የሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንን ትምህርት በሚገባ የያዘ ፣ እንዲሁም ለልዑል እግዚአብሔር ፣ ለእመቤታችን ፣ ለቅዱሳን መላእክት ፣  ለሰማዕታት ተገቢ የሆነውን ምስጋና የያዘ ነው፡፡ ከዚህም በላይ ለአራቱ የዓመቱ ወቅቶች እንዲስማማ አድርጎ ለበጋ፣ ለክረምት ፣ ለመጸውና ለጸደይ እንደሚሆን አድርጎ ከፋፍሏቸዋል፡፡

ለየበዓላቱም ተስማሚ ድርሰት መድቦላቸዋል፡፡ ይህንን ድርሰቱን በግእዝ ፣ በእዝልና በአራራይ ዜማ ያዘጋጀው ሲሆን ለነዚህም ስምንት የዜማ ምልክቶች ሠርቶላቸዋል፡፡

የቅዱስ ያሬድ ዜማ አንዴት ሁሉንም ይመስጥና ወደ አርያም በመንፈስ ይወስድ እንደ ነበር ለማስረዳት በገድሉም በሌሎችም መጻሕፍት የተመዘገቡ ታሪኮች አሉ፡፡ አንድ ቀን ንጉሥ ገብረመስቀል ፣ ንግሥቲቱ ፣ ጳጳሱ ፣ ካህናቱና ምእመናኑ በተሰባሰቡበት ቅዱስ ያሬድ ዜማውን ሲያዜም ንጉሡ በመመሰጡ የተነሣ በመሰቀል ተሰላጢኑ ጫፍ የቅዱስ ያሬድን እግር ወጋው፡፡

ነገር ግን ማንም አላወቀም ነበር፡፡ ቅዱስ ያሬድ መዝሙሩን ሲፈጽም ንጉሡ መስቀል ተሰላጢኑን ቢያነሳው የቅዱስ ያሬድ ደሙ ፈሰሰ፡፡ ንጉሡ በዚህ ደንግጦ ለዚህ ካሣ ይሆን ዘንድ የፈለግከውን ጠይቀኝ እሰጥሃለሁ ብሎ ቃል ገባለት፡፡ ቅዱስ ያሬድ ግን ከዚህ ዓለም ተለይቶ በምናኔ መኖርና መዝሙሩንም በሚገባ ማዘጋጀት እንደሚፈልግ ገለጠ፡፡

ምንም እንኳን አክሱምን ለቅቆ መውጣቱ ንጉሡን ቅር ቢያሰኘውም ቃሉን አንድ ጊዜ በመስጠቱ ምንም ሊያደርገው አልቻለም፡፡ ቅዱስ ያሬድም ከዚህ በኋላ አኩስምን ለቅቆ ወደ ስሜን ተራራ ጸለምት መጓዙ ይነገራል፡፡

በጐንደር ፎገራ በሚባል ሥፍራ ቅዱስ ያሬድ ጣዕም ያለው ዜማውን ሲዘምር ተጠምደው የሚያርሱ በሬዎች ድምፁን እየሰሙ ገበሬውን ሥራ ስለ አስፈቱት በዚህ ተናዶ ቅዱስ ያሬድን በጅራፍ እንደ ገረፈው ይነገራል፡፡ ቦታውም « ወርቀ ደም እየተባለ እስከ ዛሬ ይጠራል፡፡ ወርቃማና ንጹሕ ደሙ የፈሰሰበት ማለት ነው፡፡

ቅዱስ ያሬድ ዜማውን ያዘጋጀበት ዘመን ከ540-560 ዓ.ም ባለው ጊዜ መሆኑ ይነገራል፡፡ ዜማውን ካዘጋጀ በኋላ 11 ዓመት አስተምሯል፡፡ በእርሱ ዘመን ተሰዓቱ ቅዱሳን በሃይማኖት ችግር ምክንያት ወደ ኢትዮጵያ ተሰደው መጥተው ስለ ነበር ቅዱስ ያሬድ ከአንዱ ከአባ ጰንጠሌዎን የውጭውን ሀገር ቤተ ክርስቲያን ባሕልና ሥርዓት ይጠይቅ ነበር፡፡

በጆሮ የሰማውንም በዓይን ለማየት ሁለት ጊዜ ሮም የተባለችውን የቁስጥንጥንያ ቤተ ክርስቲያን ጐበኘሁ ይላል፡፡ «ወሪድየ ብሔረ ሮሜ ለቤተ ክርስቲያን ርዒክዋ» እንዲል፡፡ የታሪክ ምሁሩ ሥርግው ሀብለ ሥላሴ ለቁስጥንጥንያ ዜማ መነሻው ቅዱስ ያሬድ ነው ይላሉ፡፡

ለዚህም ማስረጃ የሚያደርጉት የቁስጥንጥንያን ዜማ የደረሰው ሊቅ ዜማውን አገኘው የሚባለው የቅድስት ሶፍያን ቤተ ክርስቲያን ሲዞር ከሰማው ዜማ ነው፡፡ ይህ ዘመን ደግሞ ቅዱስ ያሬድ ከተነሣበትና ወደ ሮሜ ሄድኩ ካለበት ዘመን ጋር ተመሳሳይ ነው፡፡ እናም ምናልባት ያ ሰው ዜማውን የሰማው የቅድስት ሶፍያ ቤተ ክርስቲያንን እየዞረ ሲዘምር ከነበረው ከቅዱስ ያሬድ ሳይሆን አይቀርም ይላሉ፡፡ Ancient and medival Ethiopian History/

ቅዱስ ያሬድ ማትያስና ዮሴፍ በተባሉ የአቡነ አረጋዊ ደቀ መዛሙርት መሪነት ወደ ደብረ ዳሞ ተራራ ላይ ወጥቶ ከጻድቁ ጋር በመገናኘትና የቤተ ክርስቲያኑን ሥራ እያደነቀ ዙሪያውን ከዞረ በኋላ «ዖድክዋ ወርኢኩ ሥነ ሕንፃሃ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን» ሲል ዘመረ፡፡ በዚያም ለአንድ ሳምንት ሰንብቶ ሄዷል፡፡

ቅዱስ ያሬድ ከአቡነ አረጋዊ እና ከዐፄ ገብረ መስቀል ጋር በመሆን በወሎ፣ በጎንደር፣ በሸዋ እና እስከ ጋሞጎፋ ብርብር ማርያም ድረስ በመሄድ አስተምሯል፡፡ አንዳንድ መረጃዎች የዐርባ ምንጭን ታሪክ ከቅዱስ ያሬድ፣ ከአቡነ አረጋዊ እና ከዐፄ ገብረ መስቀል ታሪክ ጋር ያያይዙታል፡፡

ሦስቱም ብርብር ማርያምን ለማየት ሄደው በነበረ ጊዜ በዛሬው ዐርባ ምንሥ አካባቢ ሠፍረው ነበር፡፡ በዚያ ቦታ ለወታደሩ የሚበቃ የሚጠጣ ውኃ በመጥፋቱ አቡነ አረጋዊ ጸልየው መሬቱን በመስቀል ቢመቱት ዐርባ ውሃዎች ፈለቁ ይባላል፡፡ ዐፄ ገብረ መስቀል የጣና ቂርቆስን ቤተ ክርስቲያንን በሚያሠራ ጊዜ በዚያ ቦታ ለሁለት ዓመት ተቀምጦ ድጓውን በማስተማሩ ምልክት የሌለው ድጓው እስከ ዛሬ በገዳሙ ይገኛል፡፡
35 views11:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-18 12:24:47 ቅዱስ ሲኖዶስ በ፯ኛ ቀን ውሎው በአራት አጀንዳዎች  ላይ ውሳኔ አሳለፈ።
(EOTC TV//ኢኦተቤ ቴቪ // ግንቦት ፰    ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም )
ዘጋቢ መ/ር ጌታቸው በቀለ
+++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++
ለኢኦተቤ ቴቪ (EOTC TV) ዕለታዊ ማብራሪያ የሰጡት ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ሰባተኛ  ቀን  የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ  በተለያዩ ጉዳዮች ውሳኔ ማሳለፉን ገልጸዋል።
ቅዱስ ሲኖዶስ ግንቦት ፱    ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም ባካሄደው ውይይት
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ትምህርቷን ለትውልዱ የታስተምርበት ተቋማት አንዱ መንፈሳዊ ኮሌጆች መሆነቸውን አውስቷል፡፡ እነዚህ  ኮሌጆች ወጥ የሆነ ሕግ ሳይኖራቸው የቆየ ሲሆን ; በቅርቡም በሐዋሳ እና በወልቂጤ የተቋቋሙት ኮሌጆች ባቀረቡት መተዳደሪያ ደንብ መሠረት፤ ቅዱስ ሲኖዶስ ውይይት አድርጎ ለሁሉም መንፈሳዊ ኮሌጆች የሚያገለግል ወጥ የሚሆን ሕግ አዘጋጅቶ ማጽደቁን ብፁዕነታቸው ገልጸዋል፡፡ 
በሌላ አጀንዳ በጀርመንና አካባቢው ሀገረ ስብከት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በጀርመን ገዳም እንዲኖራት ያቀረበው በጥናት የተደገፈ ሰነድ ጸድቋል፡፡ ከዚሁ ጋር በተጨማሪ ብፁዕ አቡነ ቴዎፍሎስ አማካኝነት በሰሜን አሜሪካ በካሊፎርኒያ የተመሠረተው የኆኅተ ሰማይ ገዳምን በተመለከተ ጉባኤው የተወያየ ሲሆን ; ብፁዕነታቸው ገዳሙ የተመሠረተበትን ሰነድ ለጥቅምት ጉባኤ ለመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት እንደሚያስረክቡ አስታውቀዋል፡፡
ጉባኤው የአእምሮ ንብረትን የተመለከተ ጉዳይም በስፋት ተወያይቷል።  ይህ ኮሚቴ በርካታ ሥራዎችን ሲሠራ የነበረ መሆኑ ታውቆ አሁንም በተጠናከረ መንገድ እንዲሠራ በጀት እንዲያዝለት ተወስኗል፡፡ በሌላ አጀንዳ የምስጢራት መፈጸሚያ የሆነው የጸሎት መጽሐፍም  እንዲታተም ተወስኗል፡፡
ጉባኤው የጡረተኞችን አበልን የተመለከተ ጉዳይም ላይ ተወያይቷል።
የጡረተኞችን አበልን የተመለከተ ተጠንቶ እንዲቀርብ በታዘዘው መሠረት ጥናቱ ቀርቦ ውይይት ተካሂዶበታል፡፡  በዕድሜያቸው በቤተክርስቲያን ሲያገለግሉ ቆይተው በአነስተኛ ደመወዝ ጡረታ የወጡ ማስተካከያ የሚደረግበት ውሳኔም ተለልፏል፡፡
የዳልሻህ ኪዳነ ምሕረት ማኅበረ ደናግል አንድነት ገዳምን የተመለከተ ቅዱስ ሲኖዶስ የተወያየበት ጉዳይ ነው፡፡ ገዳሙ ከተመሠረተ ከአንድ ሺሕ ዓመት በላይ ሆኖታል፡፡ በዚህ ገዳም ላይ ተነሥቶ የነበረው ችግር በተመለከተ ቅዱስ ተወያይቶበት የውሳኔ ሐሳብ አሳልፏ፡፡ ውሳኔውም እናቶች በጥንት ገዳሙ ሲተዳደርበት በነበረው አሠራር መሠረት እንዲቀጥል ገዳማውያን እናቶች በጥያቄያቸውም መሠረት አምልኮአቸውን እንዲፈጽሙ ውሳኔ ተወስኗል፡፡
ይህም ሰፊ ውይይት ተደርጎበት  የእናቶች ገዳም አሠራር መሠረት እናቶች በቆየው ትውፊት፣ በጥያቄያቸው መሠረትም አምልኮታቸውንን እንዲፈጽሙ በመወሰን የዕለቱ ስብሰባ ማጠናቀቁን ለኢኦተቤ ቴቪ (EOTC TV) በሰጡት ዕለታዊ ማብራሪያ አስታውቀዋል።
የብፁዕነታቸውን ማብራሪያ በዩቲዩብ ገጻችን እንድትመለከቱ እንጋብዛለን ።
EOTC TV
+++++++++++++++++++++++++++++++++++++
             


        "የቤተክርስቲያን የሆነውን ብቻ" 
          የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት
                       የዲጂታል ሚዲያ ገጾች
ለመረጃ  +251985585858
➽ የዩቲዮብ ገጻችን
http://www.youtube.com/c/eotctv
➽ የፌስ ቡክ ገጻችንን
https://www.facebook.com/eotctvchannel
➽የቴሌግራም ገጻችን
https://t.me/eotctvchannel
➽ የቲክ ቶክ ገጻችን
https://vm.tiktok.com/ZMFSxXdUf/
➽ የዩቲዮብ ገጻችን Eotc tv 2



➽የትዊተር ገጻችን
https://twitter.com/EotcT/
➽የኢንስታግራም ገጻችን
https://www.instagram.com/p/CknRF0MtB77/?igshid=MDJmNzVkMjY=
35 views09:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-17 21:47:20
ግንቦት 12 ተክለሃይማኖት ወክርስቶሰ ሰምራ ሥርዓተ ማኅሌት
 
ስምዓኒ እግዚኦ ጸሎትየ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ   ወይብጻሕ ቅድሜከ ገአርየ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ወኢትሚጥ ገጸከ እምኔየ በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ እዝነከ ኀቤየ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ  አመ ዕለተ እጼውአከ ፍጡነ ስምዓኒ  ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ለዓለም ወለዓለመ ዓለም ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል ንወድሶ ለዘሃሎ እግዚአብሔር ልዑል ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ በአሐቲ ቃል

ነግሥ
ሰላም ለአብ ገባሬ ኲሉ ዓለም ለወልድ ሰላም ወለመንፈስ ቅዱስ ሰላም ለማርያም ሰላም ወለመላእክት ሰላም ሰላም ለነቢያት ወለሐዋርያት ሰላም ለሰማእታት ሰላም ወለጻድቃን ሰላም

ዚቅ
ሰላም ለክሙ ኦ ማኅበራኒሁ ለክርስቶስ  እለ ተጋባዕክሙ ውስተ ዝንቱ ቤት  ጳጳሳት ቀሳውስት ወዲያቆናት ሰላም ለክሙ ማኅበረ ደናግል ወመነኮሳት  እለ ተመሰልክሙ ከመ መላእክት

መልክዐ ሚካኤል
ሰላም ለሕፅንከ እንተ በዲቤሁ ሕቁፍ  ጸሎተ ቅዱሳን ውኩፍ  ሚካኤል ክቡር መስፍነ ትጉሃን አዕላፍ ለረዲኦትየ ከመ ዘይሠርር ዖፍ  እንዘ ትሠርር ነዓ በክልኤ አክናፍ

ዚቅ
ወሚካኤል አሐዱ እመላእክት  እምቅዱሳን ቀደምት እስመ በዲበ ሠናይቱ ለሰብእ ተአዛዚ

ወረብ
ሚካኤል መልአክ አሐዱ አሐዱ እመላእክት
እስመ በዲበ ሠናይቱ ለሰብእ ተአዛዚ

ነግሥ
ሰላም ለገቦከ በአክናፈ ብርሃን ግልቡብ: እንተ በዲቤሁ ይጼልል መንፈሰ ኪሩብ: ሚካኤል መልአኩ ለእግዚአብሔር አብ: አጥረየ በረድኤትከ መዓርገ ስብሐት ዕፁብ  :ተክለሃይማኖት የዋህ ወብእሲ ጠቢብ

ዚቅ
ተክለሃይማኖትኒ ይቤ ነዋ ሚካኤል አሐዱ እመላእክት  እምቅዱሳን ቀደምት መጽአ ይርድዓኒ አጽንዓኒ ወይቤለኒ ኢትፍራህ ብእሴ ፍትወት አንተ ሰላም ለከ ጽናዕ ወተአገሥ  ወእንዘ ይትናገረኒ ጸናዕኩ  ወእቤሎ ንግረኒ እስመ አጽናዕከኒ  ወይቤለኒ ሶበ ተአምር ዳዕሙ ሚካኤል መልአክክሙ

ወረብ
ይቤ ነዋ ሚካኤል አሐዱ እመላእክት እምቅዱሳን ቀደምት እምቅዱሳን
መጽአ ይርድዓኒ ይቤ ተክለሃይማኖት

መልክዐ ተክለሃይማኖት
ሰላም ለዝክረ ስምከ ዘጥንተ ፊደሉ መስቀል  ስም ክቡር ወስም ልዑል ተክለሃይማኖት ማቴዎስ በዓለ ቀዳማይ ወንጌል ከመ እወድሰከ መጠነ አውሥኦተ እክል ማዕሠረ ልሳንየ ትፍታሕ ማርያም ድንግል

ዚቅ
ናሁ ዝክርከኒ ኢይጠፍዕ  ወመንፈስከኒ የዓቅቡ መላእክት በሰማያት ኢይትኃጎል ሥጋከ በዲበ ምድር ብጹዕ ብእሲ ዘይፈርሆ ለእግዚአብሔር

ወረብ
ናሁ ዝክርከኒ ኢይጠፍዕ ወመንፈስከኒ የዓቅቡ መላእክት
ኢይትኃጎል ሥጋከ ሥጋከ ተክለሃይማኖት

መልክዐ ተክለሃይማኖት
ሰላም ለልብከ ቅዱስ ወቡሩክ ዘዐቀበ ሕጎ ለወልደ ማርያም አምላክ  ተክለሃይማኖት አሐዱ እምዐሳባውያን ዘሠርክ እምይእቲ ዐስበ ፃማከ ዘኢትትኃደግ በበክ  ያስተሣትፈኒ ለፅሩዕ ሚካኤል መልአከ

ዚቅ
መላእክት ወሰብእ አሐዱ ማኅበሮሙ በእንተ መስቀሉ ለክርስቶስ አለደ መርዔተ ኮኑ

ወረብ
አሐዱ ማኅበሮሙ ክርስቶስ ሠምራ ወተክለሃይማኖት
በእንተ መስቀሉ ለክርስቶስ አሐደ መርዔተ ኮኑ

መልክዐ ተክለሃይማኖት
ሰላም ለፍልሰተ ሥጋከ እምውሳጤ ገዳም ዔላመ ወእምነ ዔላምኒ ደብረ ሊባኖስ ዳግመ ተክለሃይማኖት ባህለ ከመ ወንጌላዊ ቀደመ  እመ ረከቡ ደቂቅከ በዓለም ሕማመ  በኀቤከ አባ ይርከቡ ሰላመ

ዚቅ
ትዌድሶ ደብረ ሊባኖስ ገዳሙ  ለተክለሃይማኖት ጻድቅ መጠነ በዝኃ ሕማሙ  ትዌድሶ ደብረ ሊባኖስ ገዳሙ  እስመ በውስቴታ ተገብረ ፍልሰተ ሥጋሁ ወዓፅሙ  ትዌድሶ ደብረ ሊባኖስ ገዳሙ እምነ አድባራት ኲሎን ዘተለዓለት በስሙ  ትዌድሶ ደብረ ሊባኖስ ገዳሙ ኢየሱስ ክርስቶስ እንተ ቀደሳ በደሙ ትዌድሶ ደብረ ሊባኖስ ገዳሙ ትዌድሶ ደብረ ሊባኖስ ገዳሙ።

ዓዲ ዚቅ
ተክለሃይማኖት ድንግል ወንጹሕ ይጸርሕ እንዘ ይብል  እስመ አብርሃት ለዛቲ መካን ፈድፋደ እምኮከበ ጽባሕ።

ምልጣን
አባ አቡነ አቡነ መምህርነ እምአዕላፍ ህሩይ ሐውጽ እምሰማይ ብርሃነከ ከመ ንርዓይ አማን ተክለሃይማኖት ፀሐይ።

አመላለስ
አማን በአማን
ተክለሃይማኖት ፀሐይ

ቅንዋት፦
ነዓምን ከመ ሞተ ወተንሥአ....

https://t.me/bete_zemas
https://t.me/bete_zemas
https://t.me/bete_zemas
37 views18:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-17 14:00:13 #የቅዱሳን_ሥዕላት_ክብር

ቅዱሳን ሥዕላት የከበሩ ናቸው፡፡ ጠቀሜታቸው ከፍተኛ በመሆኑ በቤተክርስቲያን ይሣላሉ፡፡ ይሁን እንጅ ምዕመናንም ቅዱሳን ሥዕላትን ለተለያዩ አገልግሎቶች ስለሚጠቀሙባቸው እያሣሉ በቤታቸው ይገለገሉባቸዋል፡፡ እዚህ ላይ ግን ጥንቃቄ ልናደርግ ይገባል፡፡ ቅዱሳን ሥዕላት ለግድግዳ ጌጥነት የምንጠቀምባቸው አይደሉም፡፡ በክብር በተለየ ቦታ በመጋረጃ ተጋርደው ለጸሎት በምንጠቀምበት ልዩ ቦታ ላይ ሊደረጉ ይገባል፡፡ በመሆኑም አስፈላጊ ባልሆነ መንገድ መጠቀም ጉዳት እንጅ ጥቅም የለውም፡፡ አሁን በብዛት የምናስተውለው ለቅዱሳን ሥዕላቱ የምንሰጠው ክብር በጣም የቀነሰ መሆኑን ነው፡፡ ስዕላትን ለጌጥ፣ ለማስታወቂያ፣ እነዲሁም በኮፊያ እና በተለያዩ ልብሶች ላይ መጠቀም ተገቢ አይደለም፡፡

#ለጌጥነት_አለመጠቀም፡-

ብርጭቆ ላይ ለቤት ማስጌጫነት ለመኝታ ቤት ማስጌጫነት ለቤትና ለመኪና ቁልፍ መያዣነት መጠቀም፣ ለመኪና መስኮቶች ጌጥነት ተገቢ አይደለም፡፡ ምክንያቱም ለምሳሌ መኪና ውስጥ ስትመለከቱ ሲጋራ ይጨስባቸዋል ይቀደዳሉ ጫት ይቃምባቸዋል ወዘተ ስለዚህ የተከለከለ ነው፡፡

#ልብስ_ላይ_አለማድረግ፡-

ኮፊያ ከነቴራ ላይ መሣል ተገቢ አይደለም፡፡ ምክንያቱም ልብሱ ይቆሽሻል ያ ማለት ሥዕሉንም እናበላሸዋለን ማለት ነው፡፡ ሲቆሽሽ ታሽቶ ይታጠባል በዚህም የተነሣ ሥዕሉ ይላላጣል፡፡ ስለዚህ በተለይ ለክብረ በዓላት ቅዱሳን ሥዕላትን የምናሳትም ወገኖች ጥንቃቄ ብናደርግ ጥሩ ነው፡፡ ለበረከት ስንል ለመቅሰፍት እንዳይሆንብን፡፡

#ሥዕላትን_ለማስታወቂያ_አለመጠቀም፡-

አንዳንድ ነጋዴዎችና ድርጅቶች በሚያመርቱት ምርት ላይ ቅዱሳን ሥዕላትን ይጠቀማሉ፡፡ ለምሳሌ ቅዱስ ጊዮርጊስን በቅዱስ ጊዮርጊስ ቢራ ላይ እናገኘዋለን፡፡ ይህ ፈጽሞ ስህተት ነው፡፡ ሰው ይሰክራል፣ ሥዕሉን ከጠርሙሱ ልጦ ይጥለዋል፣ ሥዕሉ ተገቢ ባልሆነ ቦታ ይወድቃል፡ ሌላው ለመዝሙር ለጉባኤ እና ለመፃህፍት ፖስተር መጠቀም ተገቢ አይደለም መክንያቱም በየመንገዱ ስለመለጠፉ ስለዚህ እንደዚህ አይነት ለቅዱሳን ሥዕላት ክብርን የሚቀንሱ ነገሮችን ከመጠቀም ልንታቀብ ተገቢ ነው፡፡

(አቤል ተፈራ በላይ)
https://t.me/bete_zemas
37 views11:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-17 08:08:30 ቅዱስ ሲኖዶስ በኦሮሚያ ክልል በኢሉአባቦራ ሀገረ ስብከት መንፈሳዊ ኮሌጅ እንዲቋቋም  ተሻሽሎ የቀረበውን ጥናት መርምሮ አጸደቀ!
++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++
የርክበ ካህናት መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በ፭ኛ ቀን የዛሬው ውሎ በኦሮሚያ ክልል የሚገኘው የኢሊአባቦራ ሀገረ ስብከት አሻሽሎ ያቀረበውን የመንፈሳዊ ኮሌጅ ማቋቋሚያ ሰነድ መርምሮ ማጽደቁን የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ፀሐፊ ብፁዕ ዶ/ር አቡነ ጴጥሮስ በዕለታዊ መግለጫቸው አስታውቀዋል።

ባለፈው ጊዜ የቀረበው የኢሊአባቦራ ሀገረ ስብከት የመንፈሳዊ ኮሌጅ ማቋቋሚያ ሰነድ ተሻሽሎ እንዲቀርብ ቅዱስ ሲኖዶስ ባስቀመጠው አቅጣጫ መሠረት ተሻሽሎ መቅረቡን የገለጹት ብፁዕነታቸው በዛሬው ዕለት የኮሌጁ መቋቋም በመርህ ደረጃ በቅዱስ ሲኖዶስ የጸደቀ መሆኑን ገልጸዋል።

በተያያዘ ዜና በምዕራብ ኦሮሚያ ማዕከላዊ በሆነ ቦታ አንድ ኮሌጅ እንዲቋቋም እንዲሁም በደቡብ ጎንደር እና በሰሜን ሸዋ አህጉረ ስብከት መንፈሳዊ ኮሌጆች እንዲቋቋሙ የቀረቡ ጥናቶች በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት የትምሕርት እና ማሰልጠኛ መምሪያ ዝርዝር ጥናቱ ተጠናቆ ከነበጀቱ ለጥቅምት የሲኖዶስ ጉባኤ ተጠንቶ እንዲቀርብ ቅዱስ ሲኖዶስ የወሰነ መሆኑን አሳውቀዋል።
EOTC TV
+++++++++++++++++++++++++++++++++++++
             


        "የቤተክርስቲያን የሆነውን ብቻ" 
          የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት
                       የዲጂታል ሚዲያ ገጾች
ለመረጃ  +251985585858
➽ የዩቲዮብ ገጻችን
http://www.youtube.com/c/eotctv
➽ የፌስ ቡክ ገጻችንን
https://www.facebook.com/eotctvchannel
➽የቴሌግራም ገጻችን
https://t.me/eotctvchannel
➽ የቲክ ቶክ ገጻችን
https://vm.tiktok.com/ZMFSxXdUf/
➽ የዩቲዮብ ገጻችን Eotc tv 2



➽የትዊተር ገጻችን
https://twitter.com/EotcT/
➽የኢንስታግራም ገጻችን
https://www.instagram.com/p/CknRF0MtB77/?igshid=MDJmNzVkMjY=
39 views05:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ