2022-08-27 13:11:19
Demonology
በተለያዩ ጊዚያት ከሰይጣን ሀይል ጋር በተያያዘ ብዙ የተለያዩ ምልከታዎች አሉ።
ምልከታዎችንም በሁለት ከፍለን እንያቸው ።
1ኛ, አንዳንዶች ሰይጣንን ከእግዚአብሔር ጋር በንፅፅር ያስቀምጡታል ። እግዚአብሔር ሲዘጋ ሰይጣን የሚከፍት እንዲሁም እግዚአብሔር ሲከፍት ሰይጣን የሚዘጋ ተቃራኒ ሀይል አድርገው ይመለከቱታል።
2ኛ, ሰይጣን በእግዚአብሔር ፣በፍጥረቱ እና በቤተክርስቲያን ላይ ያለውን ተቃርኖ እና ተቃውሞ ይዘነጉታል።
ሰይጣን ከእግዚአብሔር ጋር በንፅፅር የሚቀመጥ ሀይል አይደለም ። እግዚአብሔር የከፈተውን የሚዘጋ እንዲሁም የዘጋውን የሚከፍት ሀይል የለም ። እግዚአብሔር በልዩነት የሚታይ አምላክ እንጂ በንፅፅር የምናስቀምጠው ሀይል አይደለም ። ሰይጣንን ካነፃፀርንም የምናነፃፅረው ከፍጥረት ጋር ነው ። ለምሳሌ ከቅዱሳን መላዕክት ጋር ። በመሰረቱ ፉጡር እና ፈጣሪ ሊነፃፀሩ አይችሉም ።
በሌላ ጎኑ ደግሞ የሰይጣንንም ተንኮል መዘንጋት የለብንም ።
“ነገር ግን እባብ ሔዋንን በተንኰል እንዳሳታት ምናልባት የእናንተም ልቡና ተበላሽቶ ለክርስቶስ ካላችሁ ቅንነትና ንጽሕና እንዳትወሰዱ እሠጋለሁ።”
— 2ኛ ቆሮንቶስ 11፥3 (አዲሱ መ.ት)
ከዚህ ክፍል እንደምንረዳው የሰይጣን ተንኮል እንዲሁ በቀላሉ ልናልፈው የሚገባ ገዳይ አይደለም ። ጳውሎስን ለስጋት የዳረገው ጉዳይ የሰይጣን በአማኞች ላይ ያለው ዕቅድ ነው ።
እንዲሁም ፦ “ይህንንም የምናደርገው ሰይጣን መግቢያ ቀዳዳ እንዳያገኝ ነው፤ የእርሱን ዕቅድ አንስተውምና።”
— 2ኛ ቆሮንቶስ 2፥11 (አዲሱ መ.ት)
የሰይጣን ዕቅድ ምን እንደሆነ ማወቅ መሰረታዊ ነገር ነው ። እርሱ ብቻ አይደለም ከሰይጣን ወጥመድም እራሳችንን ለመጠበቅ ነቅቶ መጠበቅ የግድ ነው ።
ስለ ሰይጣን እና አሰራሩ በመፅሐፍ ቅዱስ ውስጥ ብዙ ስፍራዎች ላይ ተፅፎ እናገኛለን ። በጣም የሚገርመው ደግሞ አሉታዊ ሆነው ከተጠቀሱት ከአንዳንድ ምግባሮች በላይ ስለ ሰይጣን መፃፉ ነው ። ይህ ደግሞ መፅሀፍ ቅዱስ ችላ ያላለው ጉዳይ መሆኑንን እንረዳለን ።
ሰይጣን የክፋት ምንጭ ቢሆንም ማንኛውም የክፋት እንቅስቃሴ ሁሉ ከሰይጣን አይደለም ።
ክፋት ባደረግን ቁጥር ደግሞ ሰይጣን አሳስቶኝ ነው እያልን ማላከክ የለብንም።
ሮሜ 7
¹⁶ ማድረግ የማልፈልገውን የማደርግ ከሆነ፣ ሕጉ በጎ እንደሆነ እመሰክራለሁ፤
¹⁷ እንዲህ ከሆነ፣ ይህን የማደርገው እኔ ራሴ ሳልሆን፣ በእኔ ውስጥ የሚኖረው ኀጢአት ነው።
¹⁸ በእኔ፣ ማለትም ኀጢአተኛ በሆነው ተፈጥሮዬ ውስጥ ምንም በጎ ነገር እንደማይኖር ዐውቃለሁ......
በመቀጠል ስለ ሰይጣን ውድቀት እና የውድቀት ምክንያት እንዲሁም ሰይጣንን እንዴት እንቃወመዋለን ?? እና መናፍስትን የማስወጣት የፀጋ ስጦታ አለ ወይ?? በሚሉ ሶስት ክፍል ሀሳቤን አቀርባለሁ ።
ይቀጥላል .......
@behayluminilu
@behayluminilu
591 viewsBa Hi, 10:11