Get Mystery Box with random crypto!

@ArtsTvWorld - Arts TV - አርትስ ቲቪ

የቴሌግራም ቻናል አርማ artstvworldtelegram — @ArtsTvWorld - Arts TV - አርትስ ቲቪ A
የቴሌግራም ቻናል አርማ artstvworldtelegram — @ArtsTvWorld - Arts TV - አርትስ ቲቪ
የሰርጥ አድራሻ: @artstvworldtelegram
ምድቦች: ያልተመደበ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 2.48K
የሰርጥ መግለጫ

Official Arts Tv World Channel
Arts Tv frequency11512V / 27500
http://www.artstv.tv
Facebook, Youtube, Instagram & Twitter
@ArtsTvWorld

Ratings & Reviews

4.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2021-12-18 13:50:05
ሰበር ዜና

የኢትዮጵያ የጸጥታ ኃይሎች ጥምረት የወልዲያ ከተማን ሙሉ በሙሉ ተቆጣጠረ::

የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት እንዳስታወቀው የኢትዮጵያ የጸጥታ ኃይሎች ጥምረት፣ በዘመቻ ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት ከተማዋን ተቆጣጥሯል።
3.9K views10:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-16 12:25:44 ኢትዮጵያን በዘር ተኮር ጭፍጨፋ ለመጠየቅ ታስቦ የነበረው ህግ መሰረዙ ይፋ ተደረገ፡፡
የኢትዮጵያ አሜሪካውያን የዜጎች ምክር ቤት ከከፍተኛ የአሜሪካ ባለስልጣናት ጋር ያደረገውን ስብሰባ መሰረት በማድረግ ሴናተር ጂም ኢንሆፍ ለምክር ቤቱ መረጃ መላኩ ታውቋል፡፡
በመረጃውም በኢትዮጵያ “የዘር ተኮር ጭፍጨፋ ተካሂዷል” በሚል ሀሰተኛ ውንጀላ ኢትዮጵያን ለመጠየቅ የሚረዳና በአሜሪካ ሴኔት ቢሮ የታሰበው ሕግ ማለትም ÷ #HR_4350 አንቀፅ_6464_ “Determination of Potential Genocide or Crimes Against Humanity” የሚለው ረቂቅ ህግ ሙሉ በሙሉ መሰረዙን ምክር ቤቱ ይፋ አድርጎል።
ታስቦ የነበረውን ህግ ለማሰረዝ በሴናተር ጂም እና በሲቪል ምክር ቤቱ መካከል አጀንዳ ሆኖ ክርክር ተደርጎበት ነበር።
የኢትዮጵያ አሜሪካውያን የዜጎች ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ዲያቆን ዮሴፍ ተፈሪ ለሴናተር ጂም ኢንሆፍ ምስጋና ማቅረባቸውን የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል፡፡
በኢትዮጵያ ላይ የተለያዩ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ጫና ለማሳደር ሲል የፕሬዚዳንት ባይደን አስተዳደር እየተከተላቸው ከነበሩት መንገዶች መካከል ይህ የተለያዩ ሚዲያዎችን የሀሰት መረጃ መሰረት አድርጎ ሲዘጋጅ የነበረው ህግ አንዱ ነበር።
3.2K views09:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-12-02 13:35:38 ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለ1 ሚሊዮን ዲያስፖራዎች ያደረጉት ጥሪ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ለ1 ሚሊዮን ዲያስፖራዎች ጥሪ አቀረቡ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ 1 ሚሊዮን ዲያስፖራ ኢትዮጵያዊያንና ወዳጆች ወደ ኢትዮጵያ እንዲገቡ የሚደረገውን ጥሪን እንዲቀላቀሉ ጠየቁ፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቲውተር ገፃቸው የአውሮፓዊያኑን አዲስ ዓመት በኢትዮጵያ ለማክበር መንግሥት ያቀደውን 1 ሚሊዮን ዲያስፖራ ኢትዮጵያዊያንና የኢትዮጵያ ወዳጆች ወደ አገር ቤት እንዲገቡ የማድረግ ጥሪን እንዲቀላቀሉ ነው የጠየቁት፡፡
3.2K views10:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-11-25 11:11:38
ሐኪም አበበች ግንባር ድረስ በመሄድ ለቁስለኛው መድሃኒት በማቅረብ ለማከም እና ስንቅ ለማቅረብ እንደሚዘምቱ አስታወቁ፡
3.3K views08:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-11-22 13:12:53 በእርዳታ ስም የሚደረግን ጣልቃ ገብነት መንግሥት አስጠነቀቀ
በእርዳታ ስም የራሳቸውን የውጭ ፖሊሲ የሚያራምዱ አንዳንድ አገራት ከድርጊታቸው ሊጠነቀቁ እንደሚገባ መንግሥት አሳሰበ፡፡

የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት በሰጠው መግለጫ ኢትዮጵያዊያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን እንዲሁም የኢትዮጵያና የእውነት ወዳጆች ሰልፍም ይህንኑ በተለያዩ ሰበቦች በኢትዮጵያ ጉዳይ ጣልቃ የመግባት ፍላጎትን የሚቃወም እንደሆነ አሳውቋል፡፡

ሰልፈኞቹ ጣልቃ የሚገቡ አገራት በኢትዮጵያ ላይ እያደረሱ ያለውን ጥፋት ሊያጤኑ እንደሚገባ ስለመግለፃቸው ሚኒስትር ዴኤታዋ ሰላማዊት ካሳ ገልጸዋል፡፡
በዲያስፖራው በኩል ኢትዮጵያን ለመደገፍ የሚስተዋለው መነሳሳት የሚደነቅ ነው ብለዋል

መንግሥት የዲያስፖራውን ተነሳሽነትና የድጋፍ ጥያቄ በማስተባበር ይሰራልም ብለዋል፡፡
አገሪቱ ላይ የሚደረገውን ጫና በራሳቸው ተነሳሽነት ለዓለም ያሳወቁ ሰልፈኞችን ተመስግነዋል፡፡
3.0K views10:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-11-22 13:12:31 በውጭ ኃይሎች ኢትዮጵያ ላይ እየተደረገ ያለው አላስፈላጊ ጫና በቃ ሊባል ይገባል -ጠ/ሚ ዐቢይ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ተደምረው ለእውነት ለቆሙ ኢትዮጵያውያን እና የአፍሪካ ቀንድ
ዳያስፖራዎች አድናቆቴን እገልጻለሁ አሉ።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትሥሥር ገጻቸው ባሰፈሩት መልእክት፣ መደመር የመከፋፈል አጥሮችን
ደርምሶ ወደ አንድነት መምጣት መሆኑን ጠቁመዋል ።
ባለፉት 3 ዓመታት ባደረግናቸው የቀጣናዊ ውሕደት ጥረቶች የሕዝብ ለሕዝብ ትሥሥር ወሳኝ ነበርም
ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በመልዕክታቸው።
በውጭ ኃይሎች ኢትዮጵያ ላይ እየተደረገ ያለው አላስፈላጊ ጫና በቃ ሊባል የሚገባው እንደሆነም
አስታውቀዋል
2.5K views10:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-11-12 20:47:31 የትምህርት ሚኒስትሩ በUNESCO አጠቃላይ ጉባኤ ላይ ምን አሉ ?

ፓሪስ ላይ 41ኛው የዩኔስኮ አጠቃላይ ጉባኤ እየተካሄደ ይገኛል።

በዚህ ጉባኤ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ የትምህርት ሚኒስትር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ንግግር አድርገዋል።

የማህበራዊ መገናኛ ዘዴዎች እና ዋና ዋና የመገናኛ ዘዴዎች መስፋፋታቸውን ተከትሎ አብዛኛው ሀገራት በተሳሳቱ መረጃዎች እና የሀሰት ዜናዎች እየተጎዱ መሆናቸውን የገለፁት ሚኒስትሩ ኢትዮጵያም በዚህ ሰለባ ከሆኑ ሀገራት መካከል አንዷ ናት ብለዋል።

ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ፦

" ሀገሬ ኢትዮጵያ የዚህ ክስተት ሰለባ ከሆኑ አንዷ ነች። የማህበራዊ መገናኛ አላግባብ መጠቀም እንደነዳጅ ለአሁኑ ግጭት መባባስ ብሎም ተነግሮ የማያቅል ጉዳት በማድረስ ንፁሃን ዜጎች ላይ ጉዳት እያደረሰ ይገኛል።

መሰረታዊ የዴሞክራሲያዊ መርሆችን ሳናናጋ የተሳሳተ የማህበራዊ መገናኛ ዜዴ አጠቃቀም እያደረሰ ያለውን ጉዳት በመቀነስ እንደ UN ቤተሰብ ጠንክረን መስራት አለብን"
2.7K views17:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-11-02 12:11:15 ግጮቶች ባሉበት አካባቢዎች ለሚማሩ የ2ኛ እና የ3ኛ ዲግሪ ተማሪዎች የትምህርት ሚኒስቴር ጥሪ
አቀረበ፡፡
የትምህርት ሚኒስቴር በፌስቡክ ገጹ እንዳስታወቀው በመቀሌ ፣ በአዲግራት፣በአክሱም ፣በራያና
በወልድያ ዩኒቨርስቲዎች የ 2ኛ እና 3ኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የነበሩ መደበኛ ተማሪዎች
በጊዜያዊነት ወደ ሌሎች ዩኒቨርስቲዎች ለመመደብ እንዲያስችል አስፈላጊውን የትምህርት
ማስረጃቸውን እንዲልኩ አሳስቧል፡፡
ሚኒስቴሩ ከዚህ ቀደም በተመሳሳይ ግጭቶች ባሉባቸው ዩኒቨርስቲዎች የዲግሪ ትምህርታቸዉን
ሲከታተሉ የነበሩ ተማሪዎችን ወደሌሎች ዩ1ኒቨርስቲዎች ለመመደብ ጥሪ አድርጎ እንደበር ይታወሳል፡፡
በመቀሌ ፣ በአዲግራት፣በአክሱም ፣በራያና በወልድያ ዩኒቨርስቲዎች ሲያስተምሩ ለነበሩ መምህራን
በሙሉ ወደ ሌሎች ዩኒቨርስቲዎች ጊዜያዊ ምደባ ለመመደብ ያስችለን ዘንድ ሚኒስቴሩ እስከ እሮብ
ድረስ ጥሪ ማድረጉ ይታወሳል፡፡
2.8K views09:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-11-02 12:10:42 የደቡብ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት የክተት ጥሪ
ሀገርን ከነ ሙሉ ክብሯ ለማቆየት ያለንን አማራጭ ሁሉ እንጠቀማለን ሲል የደቡብ ክልል መስተዳድር
ምክር ቤት አስ ታወቀ፡፡
መስተዳድሩ ባወጣው መግለጫ የክልላችን ብሄሮች፣ብሄረሰቦችና ህዝቦች የኢትዮጵያ ጠላት የሆነውን
አሸባሪው የትህነግ ሴራ በማክሸፍ የሀገራችንን ህልውና በማረጋገጥ ሂደት ውስጥ ግንባር ቀደም ተሰላፊ
ይሆናሉ ብሏል።
ባለፉት ዓመታት በክልላችን በዚህ የሽብር ቡድን አቀናባሪነት በተከሰቱ ግጭቶች የበርካታ ዜጎቻችን
ህይወት ተቀጥፏል፣ ከፍተኛ የንብረት ውድመት ደርሷል፣ ዜጎች ተፈናቅለዋል፣ ዘርፈ ብዙ ጉዳት
መድረሱ ተገልጿል።
ይህ በአጉል ተስፋ የተሞላ ቡድን አሁንም ይህን እኩይ ተግባሩን አጠናክሮ በመቀጠል በአማራና አፋር
ክልል ህዝቦች የማያቋርጥ የህልውና ስጋት ደቅኖ ይገኛል። ይህ ህገወጥ ቡድን ጠቤ ከተወሰኑ ክፍሎች
ጋር ነው ቢልም ዋነኛ ግቡ ሀገራችንን ማፍረስ እንደሆነ እሙን ነው ብሏል መግለጫው።

ዛሬ በአማራና አፋር ክልሎች የጀመረውን የሽብር፣ ግድያ፣ ማፈናቀል፣ መድፈር፣ ዘረፋና የሌብነት
ተግባር በእነዚህ አካባቢዎች ተገድቦ የሚቀር እንዳልሆነ መታወቅ አለበት ብሏል መግለጫው ።
ይህ የጥፋት ቡድን ትውልድን ሲያመክን የኖረ፣ ከውጭ ጠላት በላይ የኢትዮጵያን ክብር ያዋረደ ሰው በላ
ስርአት እስከወዲያኛው ታሪክ ሆኖ እንዲቀር የጠነከረ አንድነት ያስፈልጋል፤
ይህንን የሽብር ቡድን አምርሮ መዋጋት ደግሞ አማራጭ የሌለው ጉዳይ በመሆኑ መላው የክልላችን
ህዝቦች ቡድኑን በመገርሰስ ረገድ ሚናቸውን እንዲወጡ የክልሉ መንግስት ጥሪውን አስተለልፏል።
መስተዳድሩም የክልሉ ህዝቦች የሽብር ቡድኑን ተላላኪዎችና ሰርጎ ገቦችን መከታተልና የአካባቢን
ሰላም ከምንም ጊዜ በላይ ነቅቶ በመጠበቅ በግንባር እየተዋደቀ ላለው የሀገር መከላከያ ሰራዊት፣
ለክልል ልዩ ሃይሎች፣ ለሚሊሻዎችና ለተፈናቀሉ ወገኖች ስታደርጉ የቆያችሁትን ሁለንተናዊ ድጋፍ
አጠናክራችሁ እንድትቀጥሉ ሲል ጠይቋል፡፡
በክልላችን ያለንን ብዝሀነትን በመጠቀም ሊያባላን ያሰፈሰፈውን የጠላት ሃይል ግብአተ መሬት
ለመፈጸም መላው ህዝባችን በአንድነት እንዲንቀሳቀስ፣ የክልላችን ወጣቶችም ጀግናው የመከላከያ
ሰራዊት እንዲቀላቀሉ፣ አካባቢያቸውን ተደራጅተው በንቃት እንዲጠብቁ፣ በየደረጃው ያለው አመራርም
የክልሉን ጸጥታ አካላት፣ ወጣቶች እና ምልዓተ ህዝቡን በማስተባበር በግንባር ቀደምትነት
እንዲረባረብና ለማይቀረው ድል ያለንን ሁሉ ምንም ሳናስቀር ጠላትን ለመመከትና ሀገርን ለማዳን
በማዋል ለሚደረገው ፍልሚያ ቅድሚያ ሰጥቶ እንዲንቀሳቀስ የክልሉ መስተዳድር ምክር ቤት
መወሰኑን አስታውቋል፡፡
2.4K views09:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-11-02 12:09:59 በወሎ ግንባር በነበረው ውጊያ የውጭ ሀገር ዜጎች መሳተፋቸው
በወሎ ግንባር በነበረው ውጊያ÷ ኢትዮጵያውያን ያልሆኑ ኃይሎች ከአሸባሪው ቡድን ጋር መሳተፋቸውን
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አስታወቁ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለከፍተኛ የመንግሥት አመራሮች በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ
ሰጥተዋል።
በጦርነቱ ኢትዮጵያውያን ያልሆኑ እና የኢትዮጵያ ዝርያ የሌላቸው ነጮች እና ጥቁሮች ከአሸባሪው ቡድን
ጋር ተሳትፈው መስዋዕትነት መክፈላቸውን ነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያረጋገጡት።
የሕወሓት የሽብር ቡድን የከፈተውን ጦርነት እና ጦርነቱን እየመራበት ያለው ህዝባዊ አካሄድ
አስመልክቶ ማብራሪያ የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትሩ÷ ህዝብ ለመከላከያ ሠራዊቱ ያሳየው ድጋፍ
የሚበረታታ እንደነበር አስታውሰዋል፡፡
በቅስቀሳ የመጣውን የህዝብ ኃይል ለማስተናገድ በመንግስት በኩል በቂ ዝግጅት እንዳልነበርም
ተናግረዋል፡፡
አሁን ላይ ከዛ ሁኔታ እርምት ተወስዶ ስትራቴጂካዊ በሆነ መልኩ እየተሰራበት መሆኑንም ጠቅላይ
ሚኒስር ዐቢይ ገልጸዋል፡፡
አጠቃላይ ህዝቡ ለሠራዊቱ ያለው ድጋፍ አሁን ካለው በላይ ሊጠናከር ይገባል ያሉት ጠቅላይ
ሚኒስትሩ፤ ኢትዮጵያ የገጠመችው ጦርነት ከአንድ ወገን ጋር ብቻ እንዳልሆነ በመረዳት ዋጋ ለመክፈል
ያለውን ፍቅር በተግባር ሊገልጽ እንደሚገባ አሳስበዋል።
ካለምንም ጥርጥር ኢትዮጵያ ጦርነቱን ታሸንፋለች ሲሉ ጠቅላይ ሚሩ በመግለጫቸው አስታውቀዋል፡፡
ለማሸነፍ ቁልፉ እጃችን ላይ ነው ያለው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ÷አንድ መሆን ቀን ከሌት መስራት፣
ዋጋ ለመክፈል ዝግጁ መሆንን አካተው ገልጸዋል፡፡
የምናሸንፍበት እድል ግን የምናገኘው ከጠላት መሆኑን ጠቅሰው ÷ መረጃ እና ፕሮፓጋንዳ በመጠቀም
ማሸንፍ እንደሚቻል አንስተዋል፡፡
ጦርነት የፖለቲካ እሳቤ ማስጠበቂያ የመጨረሻ መንገድ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚንስትሩ፤ ውጊያ
በየትኛውም ሁኔታ ሊኖር እንደሚችል ገልፀው ጦርነቱን ግን ኢትዮጵያ እንደምታሸንፍ አትጠራጠሩ
ብለዋል።
2.0K views09:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ